ታሪኮች ስለ የዜጎች መገናኛ ብዙሐን
ኢትዮጵያ፤ የተባበሩት መንግስታት ድርጅት የሰብዓዊ መብት ምክር ቤት አባል ለመሆን ትመጥናለች?
በህዳር 12 2012 እ.ኤ.አ. የተባበሩት መንግስታት የሰብዓዊ መብቶች ምክር ቤት አባላት ሆነው ከተመረጡ አራት የአፍሪካ ሀገራት ውስጥ ኢትዮጵያ አንዷ ነች፡፡ ለመጪዎቹ ሶስት አመታት የተመረጡ ሌሎች ሀገራት አርጀንቲና፣ ብራዚል፣ ኮትዲቯር፣ ኢስቶኒያ፣ ጋቦን ፣ ጀርመን፣ አየርላንድ ፣ ጃፓን፣ ካዛኪስታን፣ ኬንያ ሞንቴኔግሮ፣ ፓኪስታን፣ የኮሪያ ሪፐብሊክ፣ ሴራሊዮን፣ የተባበሩት አረብ ኢመሬት፣ አሜሪካና ቬንዙዌላ ናቸው፡፡
‘ለሙሰኛ ባለስልጣን ምንም ምሕረት የለም’
የጨፌ ኦሮሚያ የዜና ምንጮቻችን ለአዲስ ነገር እንዳስታወቁት አቶ አባዱላ ገመዳ ከጠ/ሚ መለስ ዜናዊ ጋር የነበራቸው የሰመረ ግንኙነት ከተበላሸ (ፖለቲካዊ ጠቀሜታቸው ዝቅ ካለ) በኋላ ላለፉት በርካታ ዓመታት በእርሳቸው ሥም፣ በቤተሰቦቻቸውና በወዳጅ ዘመዶቻቸው አካባቢ ያከማቹትን ሃብት በጥሬ ገንዘብ፣ በአይነትና በንብረት በታማኝ የኦህዴድ ፓርቲ አባላትና በደህንነት ሠራተኞች ሲሰባሰብ ነበር፡፡ . . .”
በኪዌት ህቡዕ የትዊተር ገጽ ታላቅ ተቃውሞን እየመራ ነው
ባለፉት ጥቂት አመታት አመጸኞቹ በተቃዋሚ የፓርላማ አባላት በመመራታቸው ትችት ደርሶባቸዋል፤ በኋላ ወጣቶቹ የተቃውሞው መሪዎች ለመሆን ጥረት አድርገዋል፡፡ ይህ ለውጥ "የክብር ሰልፎች" ላይ የተሳተፉ ሰዎች ቁጥር እንዲያሻቅብ አድርጎታል፡፡ሌላው አስገራሚ የሚያደርገው ነገር ደግሞ የሁለቱም ሰልፎች ቀንና መነሻ ቦታ የተወሰነው በህቡዕ የትዊተር ገጽ መሆኑ ነው፡፡
ኢትዮጵያ አሸነፈች፤ ልጆቿም የእርግብ አሞራ እያሉ ፈነጠዙ
የወያኔ ካድሬዎችን ያህል በሕዝብ ደስታ የሚበሳጭ አንድ ፈልጎ ማግኘት ይቸግራል። ምነው ሸዋ፣ ዛሬኳ ቢተውን ምነው?! አሁን ማን ይሙት ሟቹ ጠቅላይ ሚኒስትር ለኳሱ ምን አበርክተው ነው ይሄ ሁሉ የታሪክ ሽሚያ? ማስታወሻነቱማ የሚገባው ብርድና ሃሩር ሳይል ለኣመታት መከራውን የበላው ሕዝብ ነው።
ኢትዮጵያ፤ ኢትዮጵያውያን የቡድናቸውን ማሸነፍ በጉጉት እየተጠባበቁ ነው
ምንም እንኳን የእግርኳስ ውጤት በአብዛኛው በጨዋታዎች እለት በሚፈጠሩ ክስተቶች ላይ ጥገኛ ቢሆንም ታሪክ ለኢትዮጵያ ብሄራዊ ቡድን ያደላል። የሱዳን ብሄራዊ ቡድን ከሜዳው ውጪ ከኢትዮጵያ ብሄራዊ ቡድን ጋር ባደረጋቸው ያለፉት ዘጠኝ ጨዋታዎች በአንዱም ያላሸነፈ ሲሆን በአጠቃላይ ሁለቱ ቡድኖች ለአፍሪካ ዋንጫ ለማለፍ ኢትዮጵያ ውስጥ ባደረጓቸው ሶስት የማጣሪያ ጨዋታዎች ኢትዮጵያ ሶስቱንም ጨዋታዎች አሸንፋ ሰባት ጎሎችን ተጋጣሚዋ ሱዳን ላይ ስታስቆጥር፤ የተቆጠረባት አንድ ጎል ብቻ ነው።
ኬንያ፤ ራሳቸውን ገንዘብ-ይገዛናል ብለው ያሉ ቡድኖች ‘የካምፓስ ቀውጢ-ቺኮችን ለሀብታሞች’ አቀረቡ
የካምፓስ ቀውጢ-ችኮች ለሀብታሞች (Campus Divas For Rich Men) ከ26 ዓመት በታች የሆኑ የኬንያ የዩንቨርስቲ ሴት ተማሪዎችን በማንኛውም ዕድሜ ክልል ውስጥ ያሉ ሀብታሞች ‘ለማጣበስ’ የተፈጠረ የፌስቡክ ገጽ ነው፡፡ ገጹ የተጠቀመበት መሪ ቃል “ገንዘብ-ይገዛናል” የሚል ነው፡፡
የጦማር የተግባር ቀን 2012፡ ‘የእኛ ኃይል’ በሚል መሪ ርዕስ ይከበራል
እንግዲህ ከ95 ሀገሮች የተውጣጡ ጦማሪያን በነዛ ብቁ እና ፈጣን እጆቻቸው ሊከትቡ ተዘጋጅተዋል፡፡ ለአንድ ቀን ሁሉም ስለ አንድ ተመሳሳይ ጉናይ ላይ በመፃፍና የሚያምር የታሪክ ፍሰት በመስራት በሚሊዮን ለሚቆጠሩ ተካታዮቻቸው ይጦምራሉ፡፡ ጥቅምት 15፣ 2012 – የጦማር የተግባር ቀን ! ከ2007 ዓ.ም ጀምሮ የጦማር የተግባር ቀን በጠቃሚ ጉዳዮች ላይ ንቃትን ለመፍጠር፤ የጦማር ጥቃት...
በቻይና ፡ አንድ ተማሪ የንግግር ነፃነትን ለመከላከል ጫማውን ወረወረ
አንድ የሃይናን ዩንቨርስቲ ተማሪ በኦክቶበር 7፣ 2012 ዓ.ም በቻይና የመናገር ነፃነት አለመኖርን ተቃውሞ ሲማ ናን በተባሉ ማኦይስት ሀያሲ ላይ ጫማውን ወረወረ፡፡ ጫማውንም ከመወርወሩ በፊት ‹‹ምንም እንኳን የምትናገረው ጥሩ ነገር ባይሆንም፣ ወደ ሆቴልዎት መመለስ ይችላሉ፤ ነገር ግን እኔ ንግግሩን ብቃወም ትንሽ ጨለማ ክፍል ውስጥ እንደሚዘጋብኝ እርግጠኛ ነኝ ፡፡›› ብሏል፡፡ ተማሪው ርምጃውን...
ባህሬን፤ ዴሞክራሲና እስልምና አንድ ላይ መኖር ይችላሉ?
‘በኢስላማዊ ማኀበረሰብ ዴሞክራሲ ሊኖር ይችላል? ’ዛሬ ይህ ርዕስ በባህሬናውያን ጦማሪዎች መካከል መነጋገሪያ ሆኗል፡፡
የኢትዮጵያ ሲቪል ሰርቪስ ኮሌጅ መካነ ድር ተመዘበረ
በኢትዮጵያ ዋና ከተማ አዲስ አበባ የሚገኘው የሲቪል ሰርቪስ ኮሌጅ መካነ ድር እራሳቸውን ራሳቸውን አርቲን ሐከርስ ብለው በሚጠሩ ሰርጎ ገቦች ተመዘበረ፡፡ በኢትዮጵያ የሚገኙ መካነ ድሮች ሲመዘበሩ ይህ የመጀመሪያው አይደለም፡፡ በ2012 እ.ኤ.አ ብቻ የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል ኮርፐሬሽን፣ የኢትዮጵያ ማዕከላዊ ስታስቲክስ ባለስልጣን እንዲሁም የኢትዮጵያ ንግድ ባንክና ሌሎች መካነ ድሮች ተመዝብረዋል፡፡ ይህን ተከትሎ...