· መጋቢት, 2013

ታሪኮች ስለ የዜጎች መገናኛ ብዙሐን ከ መጋቢት, 2013

በኬኒያ ቴሌቭዥን የተላለፈ የኮንዶም ማስታወቂያ የሃይማኖት ተቋማትን አስቆጣ

  27 መጋቢት 2013

በቅርቡ ለህዝብ አገልግሎት ይውል ዘንድ HIV እና ተዛማጅ በሽታዎችን ለመከላከል የተላለፈ የኮንዶም ማስታወቂያ የተለያዩ የሃይማኖት ተቋማትን ማስቆጣቱን ተከትሎ በመገናኛ ብዙሃን እንዳይተላለፍ ታገዷል፡፡ ማስታቂያው አንዲት ባለትዳር ሴት ባለቤቷ ከትዳር ውጪ በሚያደርጋቸው የግብረስጋ ግንኙነቶች ኮንዶም እንዲጠቀም ምክር ስትሰጠው የሚያሳይ ሲሆን ማስታወቂያው የኬኒያ ጤና ጥበቃ ሚኒስቴር ዩኤስ ኤድ እና ዩኬ ኤድ የገንዘብ ድጋፍ ተደርጎለት የተዘጋጀ ነው፡፡

ስለፍቅርና የፍቅር ጨዋታ ከአንጎላ

  21 መጋቢት 2013

ወጣቷ ሮዚ አልቬስ አንጎላዊ ጦማሪ (cronista) ናት፡፡ መኖሪያዋን ያደረገችው በአንጎላ ዋና ከተማ ሉዋንዳ ውስጥ ነው፡፡ “cronista” ማለት በፖርቱጋል ቋንቋ መጦመር የሚለውን ቃል ተስተካካይ ትርጉም የሚሰጥ ሲሆን - ፅሁፎቹ ባብዛኛ ጊዜ በጋዜጣ የሚታተሙ ታሪኮች አንዳንዴ እውነተኛ ተሪኮች ሌላ ጊዜ ደግሞ የፈጠራ ልብ ወለዶች ሲሆኑ ብዙውን ጊዜ የራስ ችሎታን በአጭሩ ያሳያሉ፡፡ “Sweet Cliché" በተሰኘው ጦማሯ አልቬስ አጫጫር ታሪኮችን የምትፅፍ ሲሆን፣ በአብዛኛው ስለፍቅር እና ስለፍቅር ጥብቅ ግንኙነቶች ትፅፋለች ( Bolgspot የፅሑፎቿ እንባቢዎች እድሜቸው ለፅሑፉ የሚመጥን ስለመሆኑ ያስጠነቅቃል)፡፡ከዚህ በታች ሰሞኑን በጣም አነጋጋሪ የነበረው ፅሑፏ ቀርቧል፡፡

የአንድ ቬንዙዌላዊ አገርበቀል ዩንቨርስቲ ውስጣዊ ምልከታ

የሚያድጉ ድምጾች  20 መጋቢት 2013

የቬንዙዌላ አገርበቀል ዩንቨርስቲ ተማሪ መሆን ምን ይመስላል? ከትምህርታዊ ተግባቦት የወጡ ሦስት ተማሪዎች በእያደጉ ያሉ ድምፆች ትዕይንተ ሥራ ላይ ዲጂታል ፎቶዎችን እንዴት ማንሳት፣ በይነመረብ ላይ መስቀል እና ማጋራት እንደሚቻል ለመማር ተሳትፈው ነበር፡፡ እነዚህ ሦስት ተማሪዎች፣ በዚህ ልዩ ዩንቨርስቲ ውስጥ ከቬንዙዌላ ማኅበረሰብ የተውጣጡ እና በይነባሕላዊ እና ተግባራዊ የትምህርት ዓይነቶችን እንዲለዋወጡ የሚደረገው ጥረት ማሳያ ናቸው፡፡ በመንግሥታዊው ኢንፎሴንትሮስ [es] የተሰኘ ፕሮግራም በተዘጋጀው የዩንቨርሲቲውን የሳተላይት ግንኙነት በመጠቀም ተማሪዎቹ እንቅስቃሴዎቻቸውን፣ ንብረቶቻቸውን እና አስደናቂ ውበት የተላበሰውን እና በቦሊቪያ ውስጥ 2,000 ሄክታር ላይ የተንጣለለውን ካምፓሳቸውን በበይነመበረብ አጋርተዋል፡፡

የግራዚያኒ ኀውልት ግንባታን የተቃወሙትን መንግሥት መቃወሙ የድርዜጎችን አነጋገረ

  19 መጋቢት 2013

መጋቢት 8/2005 ሰማያዊ ፓርቲ ከባለራዕይ ወጣቶች ማኅበር ጋር በመሆን የግራዚያኒን ኀውልት ግንባታ እንዲቃወሙ ኢትዮጵያውያንን ለሰልፍ ጠርቶ ነበር፡፡ ጄኔራል ግራዚያኒ ኢጣልያ ኢትዮጵያን ለአምስት ዓመታት ያክል በወረረችበት ጊዜ በርካታ ኢትዮጵያውያን እንዲጨፈጨፉ ምክንያት የሆነ ሰው ነው፡፡ በተለይም የካቲት 12/1937….. የተገደሉት ሰማዕታት ኀውልት ስድስት ኪሎ በሚባለው አካባቢ ይገኛል፡፡ ሰልፈኞቹ ከዚያ ተነስተው ወደ ጣልያን ኤምባሲ ማምራት ሲጀምሩ ያልተጠበቀ ተቃውሞ ከመንግሥት አካላት ገጠማቸው፡፡ በቦታው 43 ያክል ሰልፈኞች ታፍሰው ለእስር መዳረጋቸው አነጋጋሪ ዜና ለመሆን በቅቷል፡፡

የአድዋ ድል በዓል ጦማሪዎችን አነቃቅቶ አለፈ

  6 መጋቢት 2013

ጥቁር አፍሪቃውያን አውሮጵያውያንን ለመጀመሪያ ጊዜ በጦርነት ያሸነፉበት የአድዋ ድል 117ኛ ዓመት በዓል የካቲት 23/2005 በብሔራዊ ደረጃ ተከብሮ ውሏል፡፡ የበዓሉ አከባበር በብሔራዊ ደረጃ እዚህ ግባ በሚባል ዓይነት ሥነ ስርዓት ባይከበርም በርካታ ጦማሪዎች፣ አስተያየቶቻቸውን በመጻፍና በማኅበራዊ አውታር ገጾቻቸው ላይ በማስፈር የበዓሉን ለዛ ጠብቀው ለማለፍ ሞክረዋል፡፡