· መስከረም, 2012

ታሪኮች ስለ የዜጎች መገናኛ ብዙሐን ከ መስከረም, 2012

ኢራን ጎግል እና ጂሜል እንዳይታዩ አገደች

እገዳው የተላለፈበተት ምክንያት ህዝቡ ብዙዎች እንደ ስድብ ቃል የሚያዩት በዩቱዩብ የሚገኘውን ጸረ እስላም ፊልም እንዲቃወሙ ነው (ዩቲዩብ የጎግል ንብረት ነው)፡፡ ኮራማባዲ “የወንጀል ይዘት ያላቸው ቅጽበቶች ድንጋጌ ኮሚሽን” ቁልፍ አባል ናቸው፡፡ ይህ በእንዲህ እንዳለ እንዳንዶች የጎግል መታገድ እውነተኛው ምክንያት ከመስከረም 22 ጀምሮ ስራ ይጀመራል ተብሎ የሚጠበቀውን እስካሁን ግን ብቅ ያላለውን የኢራናውያን ብሔራዊ በየነ መረብ የበለጠ ለማስተዋወቅ ነው ሲሉ ከወዲሁ ግምታቸውን አስቀምጠዋል፡፡

ኡጋንዳ፤ ከአሥራዎቹ ዕድሜ ያልተሻገረች ሴት የአፍሪካ ትንሽዋ የፓርላማ አባል ሆነች

  27 መስከረም 2012

አፍሪካ እና የአፍሪካ ሴቶች የምር እያደጉ ነው:: የማላዊ እና የላይቤሪያ ፕሬዚደንቶች ሴቶች ናቸው:: አሁን ደግሞ ኡጋንዳ በዕድሜ ትንሽዋን የ19 ዓመትዋን ሴት የፓርላማ አባል ፕሮስኮቭያ አሌንጎት ኦሮሚያት መርጣለች::

ቻይና፤ የሳንሱር ማሽኗ ለፀረ-ጃፓን እንቅስቃሴ ሲባል ቆመ?

  18 መስከረም 2012

በቻይና እና በጃፓን መካከል የዲያኦዩ (ወይም በሌላ ስሙ ሰንካኩ) ደሴት ባለቤትነት ይገባኛል ሲያይል፣ በቻይና ባለፈው ሳምንት መጨረሻ ላይ ከ80 በላይ በሚሆኑ ከተሞች መጠነ ሰፊ ፀረ-ጃፓን ሰልፎች ተካሂደዋልል፡፡ አንዳንዶቹ ሰልፎች ወደብጥብጥ ተሸጋግረዋል፤ ነውጠኞቹ በጃፓን ስታይል የተሰሩ ምግብ ቤቶችን፣ የመገበያያ አዳራሾችን እና ሱቆችን አጥቅተዋል፣ እንዲያውም አንዳንዶቹ የጃፓን መኪናዎችን ለማቃጠል ሞክረዋል፡፡ የመስመር ላይ እንቅስቃሴዎች የቅርብ ክትትል በሚደረግበት እና የመንግስት ደህንነት ኃይሎች በከፍተኛ ሁኔታ በሚተገበርበት አገር፣ ብዙዎች ይህን ያህል አመጽ እንዴት ሊከሰት እንደቻለ ተገርመዋል፡፡

#ውድየግብጽአየርመንገድ፣ እባካችኹ የተሻለ አገልግሎት

ባለፉት ጥቂት ዓመታት አመታት ውስጥ ግልጽ ሆኗል ፤ በበቂ ሁኔታ የሚጮህ ድምጽ እና ብዙ አድማጭ ያለው አንድ ሰው ካለ (ጥሩ አሽሙርን ለመጥቀስ አይደለም) ማኀበራዊ ሚዲያ ለለውጥ እንደትልቅ አማራጭ ሊያገለግል ይችላል፤ ለውጡ አብዛኛውን ጊዜ ፖለቲካዊ ወይም ማኀበራዊ ሲሆን ታዋቂው ጦማሪ የዶሱ ሂዘር አርምስትሮንግ እንዳረጋገጠው ደግሞ ትልልቅ ኩባንያዎች ቅሬታዎን እንዲሰሙ የማደረግም አቅም አለው፡፡

ኢትዮጵያ፤ በእስር ላይ ያለውን ጦማሪ እስክንድር ነጋን ማስታወስ

  17 መስከረም 2012

ሐምሌ 6/2004 የኢትዮጵያ ፌዴራል ፍርድ ቤት ጦማሪው እስክንድር ነጋን ጨምሮ ሌሎችንም 23 የተቃውሞ ተግባር የፈፀሙ ሰዎችን ለ18 ዓመታት እና ሌላ መጠን ያለው የእስር ፍርድ ከአሸባሪነትጋ በተያያዘ በይኖባቸዋል፡፡ እስክንድር ነጋ የተቃውሞ ሐሳቦቹን መተንፈሻ ለማግኘት የመስመር ላይ ጦማሪ የሆነ ጋዜጠኛ ሲሆን መጨረሻ ጊዜ ከታሰረ አንድ ዓመት ሞላው፡፡ መስከረም 4/2005 የታሰረበት አንደኛ ዓመት ነበር፡፡ የኢትዮጵያ የኢንተርኔት ተጠቃሚ ማኅበረሰብ በፌስቡክ ላይ አስታውሶታል፡-

ሕንድ፤ ባሎች ሚስቶቻቸውን ለማጀት ሥራቸው ሊከፍሏቸው ነው?

  15 መስከረም 2012

የህንድ የሴቶችና ሕፃናት ሕብረት ዕድገት ሚኒስቴር ያወጣው ረቂቅ አዋጅ በፓርላማው ከፀደቀ፣ ሚስቶች በቤት ውስጥ ለሚሰሩት ሥራ ባሎች ውጪ ሰርተው ከሚያገኙት ውስጥ የተወሰነ መጠን ለሚስቶቻቸው እንዲከፍሉ የሚያስገድድ ይሆናል፡፡ በሚኒስቴሩ ዕቅድ መሰረት፣ ሚስቶች በቤት ውስጥ የሚሰሩት ስራ ዋጋ የሚለካበት ሞዴል የተዘጋጀ ሲሆን፣ በዚሁ መሰረት የቤት ውስጥ ሥራ የሚሰሩትን ሰዎችና ሥራቸው ለኢኮኖሚው ያለውን ተዋፅዖ ዕውቅና መስጠት ይቻላል፡፡

ኢራን፤ “የእስልምና ወታደሮች” የካርቱኒስቱን የፌስቡክ ገጽ መዘበሩ

ዝነኛው ካርቲኒስት ማና ናዬስታኒ ማክሰኞ መስከረም 11 ፣ 2012 ራሳቸውን “የእስልምና ወታደሮች” ብለው በሚጠሩ የስርዓቱ ደጋፊ ሰርጎ ገቦች ተመዘበረ፡፡ ሰርጎ ገቦቹ በራሳቸው የፌስቡክ ገጽ “ፈጣሪ ይመስገን ፤ የማና ናዬስታኒን የፌስቡክ ገጽ በቁጥጥር ስር አዋልነው” የሚል መልእክት በመለጠፍ(አሁን ተነስቷል) ደስታቸውን ገልጸዋል፡፡

ዮርዳኖስ: ፓርላማው በይነመረብን የሚገድብ አዋጅ የሚያጸድቅበት ቀን ሐዘን

አዲሱ ሕግ በይነመረብን ቅድመምርመራ እና ቁጥጥር የሚያጋልጥ ነው፤ የድረአምባዎች (websites) ባለቤቶችን በመንግስት እንዲመዘገቡ እና ‹‹ልክ እንደሌሎቹ ሕትመቶች›› ፈቃድ እንዲያወጡ ይጠይቃል፡፡ የድረአምባዎች ባለቤቶች አንባቢዎቸው ድረአምባዎቻቸው ላይ ለሚለጥፏቸው አስተያየቶች ሳይቀር ኃላፊነቱን ይወስዳሉ፡፡

ሊባኖስ፤ የመካነ ድር ዐውደ ርዕይ ለቅድመ ምርመራ

12 መስከረም 2012

ሊባኖስ ከ1940 እ.ኤ..አ ጀምሮ በሊባኖስ የተደረጉ የሳንሱር እርምጃዎችን በመስመር ላይ የሚያስቀምጥ የመረጃ ቋት የመካነ ድር ዐውድ ርዕይ ለሳንሱር በመክፈት ተኩራርታለች፡፡ ይህ መካነ ድር ይፋ የተደረገው ማርች በተሰኘ የሊባኖስ ድርጅት ሲሆን ከህዝብ ርቀው ወደተቀመጡ መረጃዎች ትኩረትን ለመሳብ ነው፡፡

ቻይና በአፍሪካ፤ እውነተኛው ታሪክ

  10 መስከረም 2012

የቻይና ትኩረት በአፍሪካ ላይ በከፍተኛ ፍጥነት የጨመረው ባለፉት ጥቂት ዓመታት ሲሆን አሁን አገሪቱን የአፍሪካ ትልቋ የንግድ ሸሪክ አድርጓታል፡፡ “በቻይና እና አፍሪካ መካከል የተደረገው የንግድ ልውውጥ ባለፉት 5 የ2012 ወሮች ውስጥ የዓመት ለዓመት ንፅፅሩ በ22 በመቶ ሲያድግ መጠኑ 80.5 ቢሊዮን ዶላር ደርሷል ” በማለት የቻይና የንግድ ሚኒስቴርን ጠቅሶ ማይክ ኪንግ ጽፏል፡፡