ታሪኮች ስለ መገናኛ ብዙሐን እና ጋዜጠኝነት
የቭየትናም አዲሱ የመረጃ መረብ ደህንነት ህግ የንግግር ነፃነትን የሚደፈጥጥና የንግድ እንቅስቃሴን የሚያውክ ነው

"እንደመንግስት ማብራሪያ ከሆነ፣ ጥብቅ ቁጥጥር የአዲሱ ህግ ዋና ሃሳብ ነው፡፡"
ኢትዮጵያውያኖች የብሔራዊ ቴሌቪዥናቸውን ‹ውሸቶች› በኤፕሪል ዘ ፉል ቀን አፌዙበት
ኢትዮጵያውያኖች የማሞኛ (አፕሪል ዘ ፉል) ቀንን በትዊተር ላይ በመንግሥት በሚተዳደረው የአገር ውስጥ ብቸኛ የቴሌቭዥን ጣቢያቸው (ኢቴቪ) ባስመሰሏቸው የውሸት አርዕስተ ዜኛዎች እንደንፁህ የወንዝ ወራጅ ውሃ በሚንኮለኮል ትዊቶች አጥለቅልቀውት እየተሳለቁ ቀኑን አክብረዋል፡፡
ኢትዮጵያዊቷ ጋዜጠኛ ርዕዮት ዓለሙ በእስር 1000 ቀን ሞላት
መጋቢት 7/2006 ኢትዮጵያዊቷ ጋዜጠኛ ርዕዮት ዓለሙ የታሰረችበት 1000ኛ ቀን ነው፡፡ ከሽብርተኝነት ጋር በተያያዘ ጥፋተኛ ተብላ የአምስት ዓመት ፅኑ እስራት ከተበየነባት ጥር 2004 ጀምሮ በእስር ላይ ትገኛለች፡፡
‘ጋናን ጡመራ’ የተሰኘ የማኅበራዊ አውታር የመጀመሪያ መሰባሰቢያ ቋት እየመተመሠረተ ነው
"በአካል የመገናኛ ስፍራው (ቋቱ) ልምድ ያላቸው የስብስቡ (ቡድኑ) አባላት ለተማሪዎች እና ለባለሙያዎች ሥልጠና መስጠት የሚያስችላቸውን ዕድል ለመስጠት ረዥም መንገድ ይጓዛል፡፡"
በኬኒያ ቴሌቭዥን የተላለፈ የኮንዶም ማስታወቂያ የሃይማኖት ተቋማትን አስቆጣ
በቅርቡ ለህዝብ አገልግሎት ይውል ዘንድ HIV እና ተዛማጅ በሽታዎችን ለመከላከል የተላለፈ የኮንዶም ማስታወቂያ የተለያዩ የሃይማኖት ተቋማትን ማስቆጣቱን ተከትሎ በመገናኛ ብዙሃን እንዳይተላለፍ ታገዷል፡፡ ማስታቂያው አንዲት ባለትዳር ሴት ባለቤቷ ከትዳር ውጪ በሚያደርጋቸው የግብረስጋ ግንኙነቶች ኮንዶም እንዲጠቀም ምክር ስትሰጠው የሚያሳይ ሲሆን ማስታወቂያው የኬኒያ ጤና ጥበቃ ሚኒስቴር ዩኤስ ኤድ እና ዩኬ ኤድ የገንዘብ ድጋፍ ተደርጎለት የተዘጋጀ ነው፡፡
እ.ኤ.አ.2012፤ የፍራንኮፎኖች አብዮት እና ማኅበራዊ ለውጥ ዓመት፡- ክፍል 1
2012 አልቋል፤ እናም ለፍራንኮፎን (የፈረንሳይ ቅኝ [የነበሩ]) አገራት የተረጋጋ 2013 በጉጉት ይጠብቃሉ፡፡ በ2012 በማሊ፣ በኮንጎ ዴሞክራቲክ ሪፐብሊክ (ኮንጎ) እና በሴንትራል አፍሪካ ሪፐብሊክ ውስጥ የትጥቅ ትግል ተካሂዷል፡፡ በሴኔጋል፣ ኩዊቤክ እና ፈረንሳይ ደግሞ ምርጫ ተካሂዷል፡፡ በቻድ፣ ማዳጋስካር እና ቶጎ ደግሞ ለውጥን የሚጠይቁ ሕዝባዊ የተቃውሞ ሰልፎች ተካሂደዋል፡፡ በርካታ ክርክሮች ስደትን፣ ምጣኔ ሀብታዊ ቀውሶችን እና እኩል የጋብቻ መብቶችን በተመለከተ ተደርገዋል፡፡ እነዚህ ሁሉ የሆኑት ዓበይት ለውጦችን ለማምጣት ሲሆን መረጃ በመለዋወጥ ዘዴ ነው፡፡
‘ለሙሰኛ ባለስልጣን ምንም ምሕረት የለም’
የጨፌ ኦሮሚያ የዜና ምንጮቻችን ለአዲስ ነገር እንዳስታወቁት አቶ አባዱላ ገመዳ ከጠ/ሚ መለስ ዜናዊ ጋር የነበራቸው የሰመረ ግንኙነት ከተበላሸ (ፖለቲካዊ ጠቀሜታቸው ዝቅ ካለ) በኋላ ላለፉት በርካታ ዓመታት በእርሳቸው ሥም፣ በቤተሰቦቻቸውና በወዳጅ ዘመዶቻቸው አካባቢ ያከማቹትን ሃብት በጥሬ ገንዘብ፣ በአይነትና በንብረት በታማኝ የኦህዴድ ፓርቲ አባላትና በደህንነት ሠራተኞች ሲሰባሰብ ነበር፡፡ . . .”
በሴኔጋል ቆዳን ‹‹ሙሉ በሙሉ ነጭ›› የሚያደርገው ክሬም ቁጣ ቀሰቀሰ
በብዙ የአፍሪካ ሀገሮች ቆዳን ማቅላት የተለመደ እና በህግም የተፈቀደ ተግባር ነው፡፡ ነገር ግን ቆዳን ለማቅላት ጥቅም ላይ የሚውሉ ክሬሞች አጠቃቀም ለጉዳት የሚያጋልጥ ነው፤ ከዚህም ጋር ተያይዞ በፊት ላይ ምልክት መተው፣...
ኢትዮጵያ፤ በእስር ላይ ያለውን ጦማሪ እስክንድር ነጋን ማስታወስ
ሐምሌ 6/2004 የኢትዮጵያ ፌዴራል ፍርድ ቤት ጦማሪው እስክንድር ነጋን ጨምሮ ሌሎችንም 23 የተቃውሞ ተግባር የፈፀሙ ሰዎችን ለ18 ዓመታት እና ሌላ መጠን ያለው የእስር ፍርድ ከአሸባሪነትጋ በተያያዘ በይኖባቸዋል፡፡ እስክንድር ነጋ የተቃውሞ ሐሳቦቹን መተንፈሻ ለማግኘት የመስመር ላይ ጦማሪ የሆነ ጋዜጠኛ ሲሆን መጨረሻ ጊዜ ከታሰረ አንድ ዓመት ሞላው፡፡ መስከረም 4/2005 የታሰረበት አንደኛ ዓመት ነበር፡፡ የኢትዮጵያ የኢንተርኔት ተጠቃሚ ማኅበረሰብ በፌስቡክ ላይ አስታውሶታል፡-