የተመረጡ ታሪኮች ስለ ቴክኖሎጂ
ታሪኮች ስለ ቴክኖሎጂ
በትልቁ የኢትዮጵያ ሐይቅ ላይ አደጋ ይዞ የመጣው አረም
የኢትዮጵያ ሕዝብ በፍጥነት በማደጉ በዚያው ልክ ፍላጎቱ እየጨመረ በመጣበት በዚህ ወቅት፣ ሐይቁ ላይ ያጠላበት አደጋ የተፈጥሮ ሀብቶች ላይ ያንዣበበው ችግር ልዩ ማሳያ ትዕምርት ሆኗል።
የኦሮሚያው ተቃውሞ #OromoProtests በተቀሰቀሰ ማግስት ኢትዮጵያ የበይነመረብ ግንኙነትን ቆለፈች
#OromoProtests content on social media has triggered many attempts by the government to limit digital traffic and block telecom services in Oromia.
የNSA ስለላን በተመለከተ ካርቱኖች ይላኩና፣ 1000 ዶላር ይሸለሙ
ዘ ዌብ ዊ ወንት ካርቱኒስቶችን፣ የዲዛይን ፈጣሪዎችን እና አርቲስቶችን መልሰን የምንታገልበት ቀን በሚል ርዕስ እ.ኤ.አ. በፌብሩዋሪ 11፣ 2014 የበይነመረብ ስለላን እና የግለሰብ ደኅንነት መብትን በተመለከተ ወጥ የካርቱኖች ውድድር ውስጥ እንዲሳተፉ እየጋበዘ ነው፡፡ ካርቱኖቹ በNSA (የአሜሪካው ብሔራዊ ደኅንነት ኤጀንሴ) ዙሪያ መረጃ ማስጨበጥ የሚችሉ እና በጥቅሉ ለሚደረጉ የበይነመረብ ስለላዎች ተጠያቂነትን የሚፈልጉ ሆነው...
የኢትዮጵያ ሲቪል ሰርቪስ ኮሌጅ መካነ ድር ተመዘበረ
በኢትዮጵያ ዋና ከተማ አዲስ አበባ የሚገኘው የሲቪል ሰርቪስ ኮሌጅ መካነ ድር እራሳቸውን ራሳቸውን አርቲን ሐከርስ ብለው በሚጠሩ ሰርጎ ገቦች ተመዘበረ፡፡ በኢትዮጵያ የሚገኙ መካነ ድሮች ሲመዘበሩ ይህ የመጀመሪያው አይደለም፡፡ በ2012 እ.ኤ.አ ብቻ የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል ኮርፐሬሽን፣ የኢትዮጵያ ማዕከላዊ ስታስቲክስ ባለስልጣን እንዲሁም የኢትዮጵያ ንግድ ባንክና ሌሎች መካነ ድሮች ተመዝብረዋል፡፡ ይህን ተከትሎ...
ኢራን ጎግል እና ጂሜል እንዳይታዩ አገደች
እገዳው የተላለፈበተት ምክንያት ህዝቡ ብዙዎች እንደ ስድብ ቃል የሚያዩት በዩቱዩብ የሚገኘውን ጸረ እስላም ፊልም እንዲቃወሙ ነው (ዩቲዩብ የጎግል ንብረት ነው)፡፡ ኮራማባዲ “የወንጀል ይዘት ያላቸው ቅጽበቶች ድንጋጌ ኮሚሽን” ቁልፍ አባል ናቸው፡፡ ይህ በእንዲህ እንዳለ እንዳንዶች የጎግል መታገድ እውነተኛው ምክንያት ከመስከረም 22 ጀምሮ ስራ ይጀመራል ተብሎ የሚጠበቀውን እስካሁን ግን ብቅ ያላለውን የኢራናውያን ብሔራዊ በየነ መረብ የበለጠ ለማስተዋወቅ ነው ሲሉ ከወዲሁ ግምታቸውን አስቀምጠዋል፡፡
ታንዛኒያ፣ ኢትዮጵያ፤ መለስ ዜናዊ ከመቃብር ውስጥ ትዊት እያደረጉ ነው
"ከዚያ በኋላ ድንገት@PMMelesZenawi (መለስ ዜናዊ) ጣልቃ ገቡ፤ ከሞት በኋላ ለታንዛኒያው የፓርላማ አባል ዢቶ ካብዌ መልስ መስጠት ጀመሩ:: @PMMelesZenawi: @zittokabwe እባክዎ ከኔ የተሻለ ይሁኑ፡፡ እዚህ ቀልድ የለም፤ ዋጋዬን ልከፍል እየተዘጋጀሁ ነው" የሚለው መልስ በታንዛኒያ ከፍተኛ ውይይት ፈጠረ::