ታሪኮች ስለ መካከለኛው ምስራቅ እና ሰሜን አፍሪካ
በትልቁ የኢትዮጵያ ሐይቅ ላይ አደጋ ይዞ የመጣው አረም
የኢትዮጵያ ሕዝብ በፍጥነት በማደጉ በዚያው ልክ ፍላጎቱ እየጨመረ በመጣበት በዚህ ወቅት፣ ሐይቁ ላይ ያጠላበት አደጋ የተፈጥሮ ሀብቶች ላይ ያንዣበበው ችግር ልዩ ማሳያ ትዕምርት ሆኗል።
ኢትዮጵያውያን #SomeoneTellSaudiArabia በሚል ስደተኞች ላይ የደረሰውን እርምጃ ተቃወሙ
ጥቅምት 25፣ 2005 ሳኡዲ አረቢያ በሕገወጥ ስደተኞች ላይ እርምጃ መውሰድ ጀመረች፡፡ ሳኡዲአረቢያ 7 ሚሊዮን የሚሆኑ የውጭ ዜጋ ሠራተኞች እና ቤተሰቦቻቸውን አስጠልላለች ተብሎ ይታመናል፡፡
ቪዲዮ፤ “ኖ ዉማን፣ ኖ ድራይቭ” ሳኡዲ አረቢያን አደመቃት
ዛሬ፣ ጥቅምት 16፣ 2006 ለሳኡዲ አራማጆች በኪንግደሙ ሴቶች መኪና እንዳይነዱ የተጣለባቸው ማዕቀብ ላይ ለማመጽ የመረጡት ቀን ነበር። የማኅበራዊ አውታር ተጠቃሚዎች በአገሪቷ ውስጥ መኪና እየነዱ ስለታዩት ሴቶች ቁጥር መጨመር በስፋት እያወሩ...
ኢራን፤ እንደወንድ እየሆንክ፣ እንደሴት ልበስ
ቀይ ቀሚስ ሻርፕ እና ዓይነ እርግብ ያደረገ አንድ ሰው በማሪቫን ከተማ መንገዶች ኩርዲስታን ግዛት ኢራን ውስጥ በፀጥታ አካላት እየታጀበ እንዲጓዝ ተደረገ፡፡ በቤት ውስጥ ፀብ ምክንያት ጥፋተኛ የተባሉ ሦስት ሰዎች በከተማው መሐል የሴት ቀሚስ አድርገው እንዲጓዙ የግዛቲቱ ፍርድ ቤት ፈርዶባቸዋል፡፡ የቅጣቱ ዓይነት ለብዙዎች ግልጽ ባይሆንም በርካቶች ግን በቅጣቱ እንዲቆጡ አነሳስቷል፡፡
ባህሬን፤ ዴሞክራሲና እስልምና አንድ ላይ መኖር ይችላሉ?
‘በኢስላማዊ ማኀበረሰብ ዴሞክራሲ ሊኖር ይችላል? ’ዛሬ ይህ ርዕስ በባህሬናውያን ጦማሪዎች መካከል መነጋገሪያ ሆኗል፡፡
ኢራን ጎግል እና ጂሜል እንዳይታዩ አገደች
እገዳው የተላለፈበተት ምክንያት ህዝቡ ብዙዎች እንደ ስድብ ቃል የሚያዩት በዩቱዩብ የሚገኘውን ጸረ እስላም ፊልም እንዲቃወሙ ነው (ዩቲዩብ የጎግል ንብረት ነው)፡፡ ኮራማባዲ “የወንጀል ይዘት ያላቸው ቅጽበቶች ድንጋጌ ኮሚሽን” ቁልፍ አባል ናቸው፡፡ ይህ በእንዲህ እንዳለ እንዳንዶች የጎግል መታገድ እውነተኛው ምክንያት ከመስከረም 22 ጀምሮ ስራ ይጀመራል ተብሎ የሚጠበቀውን እስካሁን ግን ብቅ ያላለውን የኢራናውያን ብሔራዊ በየነ መረብ የበለጠ ለማስተዋወቅ ነው ሲሉ ከወዲሁ ግምታቸውን አስቀምጠዋል፡፡
#ውድየግብጽአየርመንገድ፣ እባካችኹ የተሻለ አገልግሎት
ባለፉት ጥቂት ዓመታት አመታት ውስጥ ግልጽ ሆኗል ፤ በበቂ ሁኔታ የሚጮህ ድምጽ እና ብዙ አድማጭ ያለው አንድ ሰው ካለ (ጥሩ አሽሙርን ለመጥቀስ አይደለም) ማኀበራዊ ሚዲያ ለለውጥ እንደትልቅ አማራጭ ሊያገለግል ይችላል፤ ለውጡ አብዛኛውን ጊዜ ፖለቲካዊ ወይም ማኀበራዊ ሲሆን ታዋቂው ጦማሪ የዶሱ ሂዘር አርምስትሮንግ እንዳረጋገጠው ደግሞ ትልልቅ ኩባንያዎች ቅሬታዎን እንዲሰሙ የማደረግም አቅም አለው፡፡
ኢራን፤ “የእስልምና ወታደሮች” የካርቱኒስቱን የፌስቡክ ገጽ መዘበሩ
ዝነኛው ካርቲኒስት ማና ናዬስታኒ ማክሰኞ መስከረም 11 ፣ 2012 ራሳቸውን “የእስልምና ወታደሮች” ብለው በሚጠሩ የስርዓቱ ደጋፊ ሰርጎ ገቦች ተመዘበረ፡፡ ሰርጎ ገቦቹ በራሳቸው የፌስቡክ ገጽ “ፈጣሪ ይመስገን ፤ የማና ናዬስታኒን የፌስቡክ ገጽ በቁጥጥር ስር አዋልነው” የሚል መልእክት በመለጠፍ(አሁን ተነስቷል) ደስታቸውን ገልጸዋል፡፡
ዮርዳኖስ: ፓርላማው በይነመረብን የሚገድብ አዋጅ የሚያጸድቅበት ቀን ሐዘን
አዲሱ ሕግ በይነመረብን ቅድመምርመራ እና ቁጥጥር የሚያጋልጥ ነው፤ የድረአምባዎች (websites) ባለቤቶችን በመንግስት እንዲመዘገቡ እና ‹‹ልክ እንደሌሎቹ ሕትመቶች›› ፈቃድ እንዲያወጡ ይጠይቃል፡፡ የድረአምባዎች ባለቤቶች አንባቢዎቸው ድረአምባዎቻቸው ላይ ለሚለጥፏቸው አስተያየቶች ሳይቀር ኃላፊነቱን ይወስዳሉ፡፡