ታሪኮች ስለ እንግሊዝኛ
እ.ኤ.አ.2012፤ የፍራንኮፎኖች አብዮት እና ማኅበራዊ ለውጥ ዓመት፡- ክፍል 1
2012 አልቋል፤ እናም ለፍራንኮፎን (የፈረንሳይ ቅኝ [የነበሩ]) አገራት የተረጋጋ 2013 በጉጉት ይጠብቃሉ፡፡ በ2012 በማሊ፣ በኮንጎ ዴሞክራቲክ ሪፐብሊክ (ኮንጎ) እና በሴንትራል አፍሪካ ሪፐብሊክ ውስጥ የትጥቅ ትግል ተካሂዷል፡፡ በሴኔጋል፣ ኩዊቤክ እና ፈረንሳይ ደግሞ ምርጫ ተካሂዷል፡፡ በቻድ፣ ማዳጋስካር እና ቶጎ ደግሞ ለውጥን የሚጠይቁ ሕዝባዊ የተቃውሞ ሰልፎች ተካሂደዋል፡፡ በርካታ ክርክሮች ስደትን፣ ምጣኔ ሀብታዊ ቀውሶችን እና እኩል የጋብቻ መብቶችን በተመለከተ ተደርገዋል፡፡ እነዚህ ሁሉ የሆኑት ዓበይት ለውጦችን ለማምጣት ሲሆን መረጃ በመለዋወጥ ዘዴ ነው፡፡
“V for Vendetta” የተሰኘው ፊልም ሳንሱር አለመደረግ ቻይናውያንን አስደመመ
V for Vendetta የተሰኘው እና እ.ኤ.አ. በ2005 የተሠራው፣ ስለተበደሉ ማኅበረሰቦች የሚያወራ ልብ አንጠልጣይ ፊልም ቀድሞ በቻይና እንዳይ ታግዶ የነበረ ቢሆንም ባለፈው ባለፈው አርብ ታኅሳስ 5/2005 በቻይና የማዕከላዊ ቴሌቪዥን ጣቢያ (CCTV) ስድስተኛው ጣቢያ ታይቷል፡፡ በተለይም የመንግሥታትን ጭቆና ለመቃወም በመላው ዓለም ጭቆናን የመቋቋም ትዕምርት ሆኖ በአራማጆች የተመረጠው ‘V’ ሳይቆረጥ/ሳይወጣ መታየቱ በርካቶችን አስደምሟል፡፡.
የ‹‹ሕገ-መንግሥቱ ይከበር›› እንቅስቃሴ በኢትዮጵያ
በአዲስ አበባ የሚገኙ ወጣት ጦማሪ እና አራማጆች ከኢትዮጵያ የድርዜጎች (netizens) ጋር በማበር መንግሥታቸው የኢትዮጵያን ሕገ-መንግሥት እንዲያከብር ጠየቁ፡፡ ‹‹ሕገ-መንግሥቱ ይከበር›› የተሰኘው እንቅስቃሴ በትዊተር እና በፌስቡክ ላይ የተካሄደው የኢትዮጵያ መንግሥት ሕገ-መንግሥቱን የጣሰባቸውን መረጃዎች በመለዋወጥ ነበር፡፡
የመለስ ዜናዊ የሙት መንፈስ ኢትዮጵያውንን እያሳደደ ነው?
የቀድሞው ጠቅላይ ሚኒስትር መለስ ዜናዊ የት ይሆኑ ይሆን በሚለው ላይ ወራት የዘለቀው ግምት አቧርቶ በ57 ዓመታቸው ከዚህ ዓለም በሞት እንደተለዩ በመደበኛ መንገድ ከተገለጸ ወዲህ ሦስት ወራት ተቆጥረዋል፡፡ ቢሆንም የመለስ ዜናዊ የሙት መንፈስ በአዲስ አበባ እና በሌሎችም ዋና ዋና ከተሞች እና የገጠር መንደሮች አውራ ጎዳናዎች ላይ በተሰቀሉ ምስሎቻቸው ኢትዮጵያውያንን አጥብቀው የያዙበት እጃቸው የመላላት አዝማሚያ አላሳየም፡፡
ኢትዮጵያ፤ የተባበሩት መንግስታት ድርጅት የሰብዓዊ መብት ምክር ቤት አባል ለመሆን ትመጥናለች?
በህዳር 12 2012 እ.ኤ.አ. የተባበሩት መንግስታት የሰብዓዊ መብቶች ምክር ቤት አባላት ሆነው ከተመረጡ አራት የአፍሪካ ሀገራት ውስጥ ኢትዮጵያ አንዷ ነች፡፡ ለመጪዎቹ ሶስት አመታት የተመረጡ ሌሎች ሀገራት አርጀንቲና፣ ብራዚል፣ ኮትዲቯር፣ ኢስቶኒያ፣ ጋቦን ፣ ጀርመን፣ አየርላንድ ፣ ጃፓን፣ ካዛኪስታን፣ ኬንያ ሞንቴኔግሮ፣ ፓኪስታን፣ የኮሪያ ሪፐብሊክ፣ ሴራሊዮን፣ የተባበሩት አረብ ኢመሬት፣ አሜሪካና ቬንዙዌላ ናቸው፡፡
በኪዌት ህቡዕ የትዊተር ገጽ ታላቅ ተቃውሞን እየመራ ነው
ባለፉት ጥቂት አመታት አመጸኞቹ በተቃዋሚ የፓርላማ አባላት በመመራታቸው ትችት ደርሶባቸዋል፤ በኋላ ወጣቶቹ የተቃውሞው መሪዎች ለመሆን ጥረት አድርገዋል፡፡ ይህ ለውጥ "የክብር ሰልፎች" ላይ የተሳተፉ ሰዎች ቁጥር እንዲያሻቅብ አድርጎታል፡፡ሌላው አስገራሚ የሚያደርገው ነገር ደግሞ የሁለቱም ሰልፎች ቀንና መነሻ ቦታ የተወሰነው በህቡዕ የትዊተር ገጽ መሆኑ ነው፡፡
ኬንያ፤ ራሳቸውን ገንዘብ-ይገዛናል ብለው ያሉ ቡድኖች ‘የካምፓስ ቀውጢ-ቺኮችን ለሀብታሞች’ አቀረቡ
የካምፓስ ቀውጢ-ችኮች ለሀብታሞች (Campus Divas For Rich Men) ከ26 ዓመት በታች የሆኑ የኬንያ የዩንቨርስቲ ሴት ተማሪዎችን በማንኛውም ዕድሜ ክልል ውስጥ ያሉ ሀብታሞች ‘ለማጣበስ’ የተፈጠረ የፌስቡክ ገጽ ነው፡፡ ገጹ የተጠቀመበት መሪ ቃል “ገንዘብ-ይገዛናል” የሚል ነው፡፡
ኡጋንዳ፤ ከአሥራዎቹ ዕድሜ ያልተሻገረች ሴት የአፍሪካ ትንሽዋ የፓርላማ አባል ሆነች
አፍሪካ እና የአፍሪካ ሴቶች የምር እያደጉ ነው:: የማላዊ እና የላይቤሪያ ፕሬዚደንቶች ሴቶች ናቸው:: አሁን ደግሞ ኡጋንዳ በዕድሜ ትንሽዋን የ19 ዓመትዋን ሴት የፓርላማ አባል ፕሮስኮቭያ አሌንጎት ኦሮሚያት መርጣለች::
ቻይና፤ የሳንሱር ማሽኗ ለፀረ-ጃፓን እንቅስቃሴ ሲባል ቆመ?
በቻይና እና በጃፓን መካከል የዲያኦዩ (ወይም በሌላ ስሙ ሰንካኩ) ደሴት ባለቤትነት ይገባኛል ሲያይል፣ በቻይና ባለፈው ሳምንት መጨረሻ ላይ ከ80 በላይ በሚሆኑ ከተሞች መጠነ ሰፊ ፀረ-ጃፓን ሰልፎች ተካሂደዋልል፡፡ አንዳንዶቹ ሰልፎች ወደብጥብጥ ተሸጋግረዋል፤ ነውጠኞቹ በጃፓን ስታይል የተሰሩ ምግብ ቤቶችን፣ የመገበያያ አዳራሾችን እና ሱቆችን አጥቅተዋል፣ እንዲያውም አንዳንዶቹ የጃፓን መኪናዎችን ለማቃጠል ሞክረዋል፡፡ የመስመር ላይ እንቅስቃሴዎች የቅርብ ክትትል በሚደረግበት እና የመንግስት ደህንነት ኃይሎች በከፍተኛ ሁኔታ በሚተገበርበት አገር፣ ብዙዎች ይህን ያህል አመጽ እንዴት ሊከሰት እንደቻለ ተገርመዋል፡፡
#ውድየግብጽአየርመንገድ፣ እባካችኹ የተሻለ አገልግሎት
ባለፉት ጥቂት ዓመታት አመታት ውስጥ ግልጽ ሆኗል ፤ በበቂ ሁኔታ የሚጮህ ድምጽ እና ብዙ አድማጭ ያለው አንድ ሰው ካለ (ጥሩ አሽሙርን ለመጥቀስ አይደለም) ማኀበራዊ ሚዲያ ለለውጥ እንደትልቅ አማራጭ ሊያገለግል ይችላል፤ ለውጡ አብዛኛውን ጊዜ ፖለቲካዊ ወይም ማኀበራዊ ሲሆን ታዋቂው ጦማሪ የዶሱ ሂዘር አርምስትሮንግ እንዳረጋገጠው ደግሞ ትልልቅ ኩባንያዎች ቅሬታዎን እንዲሰሙ የማደረግም አቅም አለው፡፡