ታሪኮች ስለ ፖለቲካ

የኦሮሞ ሙዚቀኞችን የማፈን አሳፋሪ ገመና

  8 ጥር 2016

የመንግሥት ሳንሱርን ለመስበር አማራጭ ይዞ የመጣውን ኢንተርኔት በመጠቀም፣ በዚህ ጽሑፍ ጸሐፊ ዩቱዩብ እና ፌስቡክ ላይ በተደረገ ቆጠራ ብቻ ከ300 በላይ ፖለቲካ ነክ ዘፈኖች ከ2006 ወዲህ የተለቀቁ መሆኑ የፖለቲካ ዘፈኖች መነሳሳት አለ ብሎ ለማለት ያስችላል፡፡

ተማሪዎች የዋና ከተማዋን የመስፋፋት ዕቅድ ለምን ይቃወማሉ?

  12 ታሕሳስ 2015

"በዐሥር ሺሕዎች የሚቆጠሩ ገበሬዎችን የሚያፈናቅል፣ ኑሯቸውን የሚያጠፋ እና ማንነታቸውን የሚያንኳስሰውን ይህንን ዕቅድ ይዞ መቀጠል በጣም የሚያሳዝን ነው የሚሆነው፡፡ ትኩረት ሊሰጠው ይገባል፡፡ ተማሪዎች ለገበሬዎቹ ጥቅም ሲሉ ነው ሕይወታቸውን አደጋ ላይ ያስቀመጡት"

ኢትዮጵያውያኖች የብሔራዊ ቴሌቪዥናቸውን ‹ውሸቶች› በኤፕሪል ዘ ፉል ቀን አፌዙበት

  8 ሚያዝያ 2014

ኢትዮጵያውያኖች የማሞኛ (አፕሪል ዘ ፉል) ቀንን በትዊተር ላይ በመንግሥት በሚተዳደረው የአገር ውስጥ ብቸኛ የቴሌቭዥን ጣቢያቸው (ኢቴቪ) ባስመሰሏቸው የውሸት አርዕስተ ዜኛዎች እንደንፁህ የወንዝ ወራጅ ውሃ በሚንኮለኮል ትዊቶች አጥለቅልቀውት እየተሳለቁ ቀኑን አክብረዋል፡፡

የበይነመረብ ዘመቻ በኢትዮጵያ ስለ ሰላማዊ ሰልፍ እና ዴሞክራሲ

  10 ግንቦት 2013

ዞን ዘጠኝ ተብሎ በሚጠራው የጦማሪዎች እና አራማጆች ኢ-መደበኛ ቡድን አስጀማሪነት በርካታ የኢትዮጵያ ማኅበራዊ አውታር ተጠቃሚዎች ከሚያዝያ 30 እስከ ግንቦት 2/2005 ድረስ የዘለቀ የበይነመረብ ዘመቻ አድርገው ነበር (የዘመቻው ጋዜጣዊ መግለጫ እዚህ አለ)፡፡ ዘመቻው ለቡድኑ ሦስተኛው ሲሆን፣ ‹‹ዴሞክራሲን በተግባር እናውል፤ የሰላማዊ ሰልፍ መብት ይመለስ›› የሚል መሪ ቃል ላይ ተንተርሶ መንግሥት ‹‹በቀጥታና በተዘዋዋሪ›› እያደረገው ነው የተባለውን እገዳ ነገር ግን በኢትዮጵያ ሕገ መንግሥት የተፈቀደውን ‹‹ሰላማዊ ሰልፍ የማድረግ፣ የመሰብሰብና አቤቱታ የማቅረብ መብት›› ራሱ መንግሥት እንዲያከብረው የሚጠይቅ ዘመቻ ነበር፡፡ በዘመቻው የተለያዩ ጦማሮች የተጻፉ ሲሆን፣ በተወሰኑ ሰዓቶች ልዩነት አብዛኛው የዘመቻው ተሳታፊ የሚያጋራቸው አጫጭር ጽሑፎች ተለጥፈዋል፣ ተሳታፊዎች ለዘመቻው የተዘጋጀውን የፕሮፋይል ምስል እንዲቀይሩ ተጋብዘው እንደተጠየቁት አድርገዋል፣ የዘመቻውን ሒደት እንዲከታተሉ የዘመቻው የኹነት ገጽ ተፈጥሯል፣ ባለፉት ዓመታት ውስጥ የተከለከሉ ሰልፎች የጊዜ መሥመር ተዘጋጅቶ ታትሟል፤ በተጨማሪም በአንድ ደቂቃ ተኩል ቪዲዮ መብቱ ለዜጎች እንዲከበር ተጠይቋል፡፡ ከፌስቡክ በተጨማሪም በትዊተር ላይ #Demonstration4Every1 እና #Assembly4Every1 በሚሉ ኃይለ ቃሎች ተሳታፊዎች ሐሳባቸውን ገልጸዋል፡፡

ጅቡቲ፤ ‘ዲሞክራሲያዊ’ ምርጫን ተከትሎ የመጣው እስር

  11 ሚያዝያ 2013

ትንሽ አገር ነገር ግን በአፍሪካ ቀንድ እጅግ በጣም ስትራቴጂክ አገር በሆነችው ጅቡቲ የየካቲት 15፣ 2005 አገር አቀፋዊ ምርጫን ተከትሎ በተደረገ የተቃውሞ ሰልፍ የተቃዋሚ ፓርቲ መሪዎች ታሰሩ፡፡ በምርጫው ‹የሕዝቦች አንድነት ለዕድገት› (People's Rally for Progress) የተሰኛው ፓርቲ በድጋሚ ድልን ተቀዳጅቷል፡፡ ፕሬዝዳንት እስማኤል ኡመር ጉሌህ ጅቡቲን እ.ኤ.አ ከ1999 ጀምሮ የመሩ ሲሆን በምርጫውም የ80 በመቶ መራጮች ድምፅ ቢያገኙም በከፍተኛ ሁኔታ በማጭበርበር ተጠርጥረዋል፡፡ እስሩ የመጣውም በዚሁ ማጭበርበር ጉዳይ [fr] ላይ ዜጎች ሰልፍ በመውጣታቸው ነው፡፡ እንደየጅቡቲ ሰብኣዊ መብት ሊግ እና የዓለምአቀፍ ሰብኣዊ መብት ፌደሬሽን ከሆነ 90 ሰዎች በአሰቃቂነቱ በሚታወቀው ጋቦዴ ማዕከላዊ እስር ቤት ታጉረዋል፡፡ እስሩ ይህ ጽሑፍ እስከተጻፈበት ሚያዚያ 20005 ድረስ ቀጥሏል፡፡

የአድዋ ድል በዓል ጦማሪዎችን አነቃቅቶ አለፈ

  6 መጋቢት 2013

ጥቁር አፍሪቃውያን አውሮጵያውያንን ለመጀመሪያ ጊዜ በጦርነት ያሸነፉበት የአድዋ ድል 117ኛ ዓመት በዓል የካቲት 23/2005 በብሔራዊ ደረጃ ተከብሮ ውሏል፡፡ የበዓሉ አከባበር በብሔራዊ ደረጃ እዚህ ግባ በሚባል ዓይነት ሥነ ስርዓት ባይከበርም በርካታ ጦማሪዎች፣ አስተያየቶቻቸውን በመጻፍና በማኅበራዊ አውታር ገጾቻቸው ላይ በማስፈር የበዓሉን ለዛ ጠብቀው ለማለፍ ሞክረዋል፡፡

የ2013ቱን የአፍሪካ አገራት ዋንጫ ኢትዮጵያውያን በተለያየ ባንዲራ ውልብልቢት እያደመቁት ነው

  25 ጥር 2013

በመላው ዓለም ያሉ ኢትዮጵያውን የኢትዮጵያ ብሔራዊ እግር ኳስ ቡድን ከባለፈው ዓመት የ2012 የአፍሪካ አገራት ዋንጫ ሻምፒዮን ጋር በኔልስፕሩት፣ ደቡብአፍሪካ ያደረገውን ከባድ ግጥሚያ በድምቀት እያከበሩ ነው፡፡ ከኢትዮጵያውያኑ ውብ አጨዋወት እና ከረዥም ጊዜ መጥፋት በኋላ በአፍሪካ ዋንጫ ከታየው ድንቅ የተጫዋቾች ችሎታ ባሻገር፣ የኢትዮጵያ ፖለቲካ ከኳሱ ጎንለጎን ማዕከላዊ የውይይት አጀንዳ ለመሆን በቅቶ ነበር፡፡ በስታዲየሙ ጨዋታውን ለመመልከት የገቡት ኢትዮጵያውያን የተለያዩ ጽሑፎችን እና ባንዲራዎችን ሲያውለበልቡ ታይተዋል፡፡