ታሪኮች ስለ ዓለም አቀፍ ግንኙነቶች ከ መጋቢት, 2013

የግራዚያኒ ኀውልት ግንባታን የተቃወሙትን መንግሥት መቃወሙ የድርዜጎችን አነጋገረ

  19 መጋቢት 2013

መጋቢት 8/2005 ሰማያዊ ፓርቲ ከባለራዕይ ወጣቶች ማኅበር ጋር በመሆን የግራዚያኒን ኀውልት ግንባታ እንዲቃወሙ ኢትዮጵያውያንን ለሰልፍ ጠርቶ ነበር፡፡ ጄኔራል ግራዚያኒ ኢጣልያ ኢትዮጵያን ለአምስት ዓመታት ያክል በወረረችበት ጊዜ በርካታ ኢትዮጵያውያን እንዲጨፈጨፉ ምክንያት የሆነ ሰው ነው፡፡ በተለይም የካቲት 12/1937….. የተገደሉት ሰማዕታት ኀውልት ስድስት ኪሎ በሚባለው አካባቢ ይገኛል፡፡ ሰልፈኞቹ ከዚያ ተነስተው ወደ ጣልያን ኤምባሲ ማምራት ሲጀምሩ ያልተጠበቀ ተቃውሞ ከመንግሥት አካላት ገጠማቸው፡፡ በቦታው 43 ያክል ሰልፈኞች ታፍሰው ለእስር መዳረጋቸው አነጋጋሪ ዜና ለመሆን በቅቷል፡፡