ሕዳር, 2012

ታሪኮች ከ ሕዳር, 2012

የመለስ ዜናዊ የሙት መንፈስ ኢትዮጵያውንን እያሳደደ ነው?

የቀድሞው ጠቅላይ ሚኒስትር መለስ ዜናዊ የት ይሆኑ ይሆን በሚለው ላይ ወራት የዘለቀው ግምት አቧርቶ በ57 ዓመታቸው ከዚህ ዓለም በሞት እንደተለዩ በመደበኛ መንገድ ከተገለጸ ወዲህ ሦስት ወራት ተቆጥረዋል፡፡ ቢሆንም የመለስ ዜናዊ የሙት መንፈስ በአዲስ አበባ እና በሌሎችም ዋና ዋና ከተሞች እና የገጠር መንደሮች አውራ ጎዳናዎች ላይ በተሰቀሉ ምስሎቻቸው ኢትዮጵያውያንን አጥብቀው የያዙበት እጃቸው የመላላት አዝማሚያ አላሳየም፡፡

30 ሕዳር 2012

የትርጉም መርሐ ግብር፤ ዓለምአቀፍ የበየነ መረብ ነጻነትን ጥበቃ መግለጫ

ለተከታዮቹ ሰባት ቀናት የዓለም ድምፆች የቋንቋ በጎ ፈቃደኞች፤   ህዝባዊ የመስመር ላይ የድጋፍ ፊርማን ይተረጉማሉ፡፡ ፊርማው በመጪው ዓለም አቀፍ የቴሌኮሚኒኬሽን ህብረት (አይቲዩ) ጉባኤ ላይ የመስመር ላይ ሰብዓዊ መብት ጥበቃን የሚደግፍና የአይቲዩ...

24 ሕዳር 2012

ኢትዮጵያ፤ የተባበሩት መንግስታት ድርጅት የሰብዓዊ መብት ምክር ቤት አባል ለመሆን ትመጥናለች?

በህዳር 12 2012 እ.ኤ.አ. የተባበሩት መንግስታት የሰብዓዊ መብቶች ምክር ቤት አባላት ሆነው ከተመረጡ አራት የአፍሪካ ሀገራት ውስጥ ኢትዮጵያ አንዷ ነች፡፡ ለመጪዎቹ ሶስት አመታት የተመረጡ ሌሎች ሀገራት አርጀንቲና፣ ብራዚል፣ ኮትዲቯር፣ ኢስቶኒያ፣ ጋቦን ፣ ጀርመን፣ አየርላንድ ፣ ጃፓን፣ ካዛኪስታን፣ ኬንያ ሞንቴኔግሮ፣ ፓኪስታን፣ የኮሪያ ሪፐብሊክ፣ ሴራሊዮን፣ የተባበሩት አረብ ኢመሬት፣ አሜሪካና ቬንዙዌላ ናቸው፡፡

16 ሕዳር 2012

‘ለሙሰኛ ባለስልጣን ምንም ምሕረት የለም’

የጨፌ ኦሮሚያ የዜና ምንጮቻችን ለአዲስ ነገር እንዳስታወቁት አቶ አባዱላ ገመዳ ከጠ/ሚ መለስ ዜናዊ ጋር የነበራቸው የሰመረ ግንኙነት ከተበላሸ (ፖለቲካዊ ጠቀሜታቸው ዝቅ ካለ) በኋላ ላለፉት በርካታ ዓመታት በእርሳቸው ሥም፣ በቤተሰቦቻቸውና በወዳጅ ዘመዶቻቸው አካባቢ ያከማቹትን ሃብት በጥሬ ገንዘብ፣ በአይነትና በንብረት በታማኝ የኦህዴድ ፓርቲ አባላትና በደህንነት ሠራተኞች ሲሰባሰብ ነበር፡፡ . . .”

13 ሕዳር 2012

በኪዌት ህቡዕ የትዊተር ገጽ ታላቅ ተቃውሞን እየመራ ነው

ባለፉት ጥቂት አመታት አመጸኞቹ በተቃዋሚ የፓርላማ አባላት በመመራታቸው ትችት ደርሶባቸዋል፤ በኋላ ወጣቶቹ የተቃውሞው መሪዎች ለመሆን ጥረት አድርገዋል፡፡ ይህ ለውጥ "የክብር ሰልፎች" ላይ የተሳተፉ ሰዎች ቁጥር እንዲያሻቅብ አድርጎታል፡፡ሌላው አስገራሚ የሚያደርገው ነገር ደግሞ የሁለቱም ሰልፎች ቀንና መነሻ ቦታ የተወሰነው በህቡዕ የትዊተር ገጽ መሆኑ ነው፡፡

11 ሕዳር 2012