- Global Voices በአማርኛ - https://am.globalvoices.org -

ለዞን ዘጠኝ ጦማሪያን እና ጋዜጠኞች ድጋፍ እና አጋርነት ለማሳየት ለሀምሌ 24 በተዘጋጀው ትዊተር ማራቶን ላይ በመካፈል አጋርነቶዎን በተግባር ያሳዩ::

Categories: ኢትዮጵያ, ሕግ, የንግግር ነፃነት, የዜጎች መገናኛ ብዙሐን, ዲጂታል አራማጅነት, 'የዓለም ድምጾች' ማስተጋቢያ, 'የዓለም ድምጾች' አድቮኬሲ
Free Zone9 Tumblr collage. Images used with permission.
 የዞን ዘጠኝ ጦማሪያን ይፈቱ ከሚለው የተምብለር ዘመቻ በፍቃድ የተወሰደ
በአወዛጋቢው የጸረ ሽብር አዋጁ እና ህገ መንግስቱን በሀይል ለመናድ በመሞከር ወንጀሎች [1] ስልጣን ላይ ባለው የኢትዮጵያ መንግስት ተጠርጥረው  በእስር  ላይ ለሚገኙት  የዞን ዘጠኝ ጦማሪያን እና ጋዜጠኞች ድጋፍ  እና አጋርነት ለማሳየት ሀምሌ 24 የትዊተር ላይ ማራቶን ተዘጋጅቷል:: ይህንንም ማራቶን በመቀላቀል  ለጦማርያኑ እና ለ ጋዜጠኞቹ ያሎትን አጋርነት በተግባር ያሳዩ::

የአለም አቀፍ የጦማርያን ማህበረሰብ  የሞያ አጋሮቻችን   የሆኑት የዞን ዘጠኝ ጦማሪያን  እና ጋዜጠኞች  በሀገራቸው  ጉዳዮች ላይ የሰለጠነ ማህበራዊ ተዋስኦ እንዲኖር ጠንክረው ከመስራት ባለፈ  ምንም የሰሩት ወንጀል ስለሌለ ፍትህ እንዲያገኙ አጥበቀን እንጠይቃለን:: የአጋሮቻችን እስር በአለም አቀፍ ደረጃ ስምምነት የተደረሰባቸውን  ሰበአዊ እና ዲሞክራሲያዊ  መብቶቻቸውን የሚደፈጥጥ ከመሆኑ ባሻገር ጦማሪያኑ እና በጋዜጠኞቹ ላይ የተመሰረቱባቸው ክሶች ኢፍትሀዊ  ናቸው ብለን እናምናለን:: የዞን ዘጠኝ ጦማሪያን እና ጋዜጠኞች የፍርድ ሂደት እየተከታተለ የሚዘግብ ድረገጽን [2] በመመልከት ስለ ጉዳዩ ያሎትን ግንዛቤዎት ያስፉ::

 ጦማሪያኑ እና ጋዜጠኞቹ  ሀምሌ 28 2006 በልደታ ከፍተኛ ፍርድ ቤት ይቀርባሉ::  ፍርድ ቤት እስከ መገኛቸው ቀን እና ከዚያም በኋላ ባሉት ግዚያት የሞያ አጋሮቻችን የኛን ከፍተኛ ድጋፍ  ይሻሉ::  በመሆኑም ሀሙስ ሀምሌ 24 2006 በመላው አለም የምንገኝ ጦማሪያን: ጻህፍት እና የማህበራዊ ሚዲያ ባለሞያዎች ይህንን  የድጋፍ መልእክት በየቋንቋችን ትዊተርን በመጠቀም ለማህበረሰብ መሪዮች: ለመንግስት ባለስልጣናት እና ለዲፕሎማሲያዊ ማህበረሰብ አባላት እናስተላልፋለን::  ይህንንም በማድረግ የተለያዩ  አለም አቀፍ መገናኛ ብዙሃን ለጉዳዩ ትኩረት እንዲሰጡት እናደርጋለን::

 ትዊተር ላይ የትኩረት ትእምርት የሆነውን የመሳላል ምልክትን እና የዞን ዘጠኝ ጦማሪያን ነጻ ይውጡ በእንግሊዘኛ #FreeZone9Bloggers:  በአለም አቀፍ ደረጃ የሚመራ የትኩረት ትእምርት እንዲሆን በትዊተር ማራቶን ላይ በመሳተፍ የዞን ዘጠኝ ጦማሪያን  እና ጋዜጠኞች እንዲፈቱ በሚከተለው  መራሀግብር  መሰረት ይጠይቁ::  

ቀን: ሀሙስ  ሃምሌ 24፣2006

ሰአት: ጠዋት ከ4:00 ሰአት እሰከ ከሰአት 8:00 በየትኛውም የግዜ ስራት ውስጥ ይሰራል::

የትኩረት ትእምርት:  #FreeZone9Bloggers:  

 አስተናጋጆች:: ኑዋቹኩ ኢግቡንኪ @feathersproject [3] ነደሳንጆ ማቻ  @ndesanjo [4] ኢለሪ ሮበርትስ  @ellerybiddle [5]

 ይህንን የትዊተር ላይ ማራቶን  ሃሙስ ለት መቀላቀል ይፈልጋሉ ? ወይ ዜናውን ለወዳጅ ዘመዶዎ ማጋራት ይፈልጋሉ? ስሞዎትን እና የትዊተር አዳራሻዎን በማህበረሰባችን የእቅድ ገጽ [6] ላይ ማስፈር ይችላሉ::

 ምሳሌዎች

 የዞን ዘጠኝ ጦማሪዎች ፍትህ ይገባቻዋል!

መጦመር ወንጀል አይደለም በመሆኑም የዞን ዘጠኝ ጦማሪዎች እና ጋዜጠኞች ይፈቱ

ስለ ሚያገባን እንጦምራለን::  

የዞን ዘጠኝ ጦማሪዎች እና ጋዜጠኞች መታሰር የአፍሪካ የሰብአዊ እና የህዝቦች መብቶች  ቻርተር መጣስ  ነው::  

የዞን ዘጠኝ ጦማሪዎች እና ጋዜጠኞች መታሰር አለም አቀፉን የሲቪል እና የፓለቲካ መብቶች ስምምነት መጣስ  ነው::  

ጣቶች እስኪዝሉ እና  የዞን ዘጠኝ ጦማሪዎች እና ጋዜጠኞች  ፍትህ እስኪያገኙ  ትዊቶች ለመጻፍ አይታክቱ:: ፍትህ ለዞን ዘጠኝ ጦማሪዎች እና ጋዜጠኞች !