ጥቅምት 25፣ 2005 ሳኡዲ አረቢያ በሕገወጥ ስደተኞች ላይ እርምጃ መውሰድ ጀመረች፡፡ ሳኡዲአረቢያ 7 ሚሊዮን የሚሆኑ የውጭ ዜጋ ሠራተኞች እና ቤተሰቦቻቸውን አስጠልላለች ተብሎ ይታመናል፡፡ የሳኡዲ አረቢያ መንግሥት ለሕገወጥ ስደተኞች የዘጠኝ ወር የእፎይታ (amnesty) ጊዜ በሚያዝያ ወር 2005 ሕጋዊ ዕውቅና እንዲያገኙ አሊያም አገሪቷን እንዲለቁ ሰጥቶ ነበር፡፡
ከሰሃራ በታች የምትገኘዋ የኢትዮጵያ ስደተኞች በዚህ የመንግሥት እርምጃ በፅኑ ከተቸገሩት ውስጥ ይመደባሉ፣ ይህም ዓመፅ እና ብጥብጥ አስከትሏል፡፡ የኢትዮጵያ መንግሥት በሳኡዲአረቢያ በሕገወጥ መንገድ የሚኖሩትን ሰዎች በሳኡዲ ፖሊሶች አንድ ኢትዮጵያዊ መገደሉ ከተነገረ በኋላ [1]ወደአገራቸው መመለስ ጀምሯል፡፡
በተለያዩ የዜና እና የማኅበራዊ አውታሮች እንደተገለጸው ከሆነ የኢትዮጵያው የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ቴድሮስ አድሃኖም የሳኡዲ አረቢያን ሕገወጥ ስደተኞችን የማስወጣት መብት ቢያምኑም [1] የኃይል አጠቃቀማቸው እና ሴቶች ላይ የደረሰው የመድፈር ድርጊትን አውግዘዋል፡፡
ከታች የሚታየው ቪዲዮ [2] በአምሃሪክትዩብ [3] የተለጠፈ ሲሆን ከሳኡዲ አረቢያ የሕገወጥ ስደተኞችን መመለስ ያሳያል፡-
MoveOn.org የተባለ ድረገጽ ላይ ፊርማ የማሰባሰብ [4] ሥራ የተጀመረ ሲሆን ለተባበሩት መንግሥታት እና እንደ አምነስቲ ኢንተርናሽናል ላሉ የሰብኣዊ መብቶች ድርጅቶች በሳኡዲ አረቢያ ስለኢትዮጵያውያን ስደተኞች አያያዝ ለማሳወቅ ታቅዷል፡፡
ኢትዮጵያውያን እና የኢትዮጵያ ወዳጆች በበይነመረብ #SomeoneTellSaudiArabia [5] የሚል ኃይለ ቃል በመጠቀም በሳኡዲ አረቢያ ያለውን የኢትዮጵያውያን ስደተኞችን አያያዝ አውግዘዋል፡፡
ማሕሌት (@Mahlet_S [6]) ስደተኞች ወንጀለኞች ሳይሆኑ ሥራ ፈላጊዎች መሆናቸውን አስታውሳለች፡-
#SomeoneTellSaudiArabia [7] ስደተኞች አገራቸው የገቡት ሥራ ፍለጋ እና ለእንጀራ እንጂ ወንጀለኛ አለመሆናቸውን ለሳኡዲአረቢያ ሊነገራት ይገባል፡፡
— Mahlet (@Mahlet_S) November 11, 2013 [8]
አዲስ ስታንዳርደ (@addisstandard [9]) የተሰኘ ወርሓዊ የኢትዮጵያ መጽሔት ደግሞ፡-
#SomeoneTellSaudiArabia [7] ሰው መሆን ማለት ምን ማለት እንደሆነ ለመረዳት ከሃይማኖታዊ ቀናተኛነት ይልቅ ሰብኣዊ ሞራል ይጠይቃል፡፡
— Addis Standard (@addisstandard) November 12, 2013 [10]
አንዳንዶች ደግሞ በኢትዮጵያ እና ኢስላም መካከል ያለውን ታሪካዊ ግንኙነት አስታውሰዋል፡፡ ሐፍሳ መሐመድ (@hafsamohamed1 [11]) የሚከተለውን ጠቁሟል፡-
#SomeoneTellSaudiArabia [7] ነብዩ መሐመድ (ሰዐወ)ተከታዮቻቸው ኢትዮጵያን እንዳያስከፉ ተናግረዋል፡፡ እነርሱ ግን ዘነጉት፡፡ #Ethiopia [12]. pic.twitter.com/XxZocICmPr [13]
— Hafsa Mohamed (@hafsamohamed1) November 12, 2013 [14]
ካሊ (@KaliDaisyy) የጻፈው [15]:-
#SomeoneTellSaudiArabia [7] ኢትዮጵያ ከመካ ለመጡት እና በቁራይሽ ጎሳ ለተከሰሱት የሙስሊም ስደተኞች እጆቿን ዘርግታ ነበር፤ እና አሁን እነርሱ ይገድሉናል?
— Kali (@KaliDaisyy) November 12, 2013 [16]
የሥነ ልቦና ባለሙያው አንቶኒዮ ሙላቱ (@AntonZfirst [17]) በነብዩ መሐመድ ስለኢትዮጵያ የተሰጠውን ምክር ማጣቀስ መርጧል፡-
1/ #SomeonetellSaudiArabia [18] ነብዩ መሐመድ እንዳሉት ‹‹ከፈለጋችሁ ወደኢትዮጵያ ሂዱ፡፡ እዚያ ማንንም የማይጎዳ ንጉሥ አለ፡፡››
— Antonio Mulatu (@AntonZfirst) November 12, 2013 [19]
በኢትዮጵያ እና በሙስሊሞች መካከል ያለው ግንኙነት የሚጀምረው ኢትዮጵያ በመካ ገዢዎች ተሰደው ለመጡት ሙስሊሞች ሠላማዊ መሸሸጊያ [20] ስትሰጥ ነው፡፡ ቢላል ኢብን አል ሐበሽ [21] ከቀደምት የመሐመድ ተከታዮች አንዱ እና የመጀመሪያ ሙኧዚን (የአዛን ዜማ አሰሚ) ሲሆን ኢትዮጵያዊ ነው፡፡
በኢስላም አራተኛ ቅዱስ ከተማ [22] የምትባለዋ ሐረር ከተማ በኢትዮጵያ ነው የምትገኘው፤ 82 መስኪዶች፣ ሦስቱ ከ10ኛው ክፍለዘመን ጀምሮ ያሉ ሲሆን 102 መስገጃዎችም አሏት፡፡
ኢትዮጵያ ከዚህም በተጨማሪ በእስልምና ታሪክ የመጀመሪያው ሒጅራ [23] (የሙስሊሞች ስደት ከክስ ሽሽት) የተካሄደባት አገር ናት፡፡
በሌላ በኩል አኑፍ (@anoofesh [24]) ከሪያድ፣ ሳኡዲ አረቢያ የኢትዮጵያዊ ስደተኞች በሳኡዲ አረቢያ እና የያኔዎቹ የሳኡዲ አረቢያ እና ሙስሊም ስደተኞች በኢትዮጵያ መካከል ያለውን ልዩነት በተመለከተ ልዩነቱን ተናግሯል፡-
@KaliDaisyy [25] ሙስሊሞች ስደተኞች ግን ኢትዮጵያ ውስጥ የነበሩት በሕገ ወጥ መንገድ አልነበረም 🙂
— anoof (@anoofesh) November 12, 2013 [26]
መላክ መኮንን (@melak_m [27]) ያንን በተመለከተ፡-
#SomeoneTellSaudiArabia [7]: ሕገ ወጥ ስደትን መከላከል ይቻላል፤ ነገር ግን በመደብደብ፣ በመግደልና በማሰር አይደለም!
— Melak Mekonen (@melak_m) November 12, 2013 [28]
የእንግሊዙ ሪስፔክት ፓርቲ ሊ ጃስፐር (@LeeJasper [29]) ደግሞ የኢትዮጵያውያን ስደተኞቹን ጉዳይ በእስራኤል ይዞታ ካሉት ፍልስጤማውያን ጋር አነጻጽራዋለች፡-
#SomeoneTellSaudiArabia [7] that their racist treatment of #Ethiopians [30] is in many ways just as bad as #Israeli [31] treatment of #Palestinians [32].
— Lee Jasper (@LeeJasper) November 12, 2013 [33]
የجبرتينهو (@iabj [34]) አስተያየት ደግሞ፡-
#SomeoneTellSaudiArabia [7] የውጭ ዜጎች ባርያዎች አይደሉም፣ ድህነትም እንከን አይደለም፡
— جبرتينهو (@iabj) November 12, 2013 [35]
በጄኔቫ፣ ስዊዘርላንድ የሰብኣዊ መብት ባለሙያው ይሄነው ዋለልኝ (@YeheneWalilegne [36]) የሳኡዲ አረቢያን ለተባበሩት መንግሥታት የሰብኣዊ መብት ቆንስላ እጩ ሆና መቅረብ ተቃውሟል፡-
#SomeoneTellSaudiArabia [7] #UNGA [37] የተባበሩት መንግሥታት የሳኡዲ አረቢያን የሰብኣዊ መብት ቆንስላው ሆና መታጨት ውድቅ ሊያደርጉት ይገባል፡፡ አለዚያ የመንግሥታቱ እና የቆንስላው ታማኝነት ጥያቄ ውስጥ ይወድቃል፡፡
— Yehenew Walilegne (@YeheneWalilegne) November 12, 2013 [38]
ሕዳር 3፣ 2006 ግን ሳኡዲ አረቢያ፣ ቻይና፣ ራሺያ እና ኩባ የሰብኣዊ መብት ቆንስላውን መቀመጫዎች ማሸነፍ ችለዋል [39]፡
አኑፍም ለኢትዮጵያውያን እንዲህ ብሏል፡-
@KaliDaisyy [25] ምን ያህል ክፉ እንደሆንን እና እንደተበሳጫችሁብን ልትነግሩን ብቻ ትፈልጋላችሁ፡፡ ብዙዎቻችሁ ምን እየተካሄደ እንደሆነ እንኳን አታውቁም፡፡ #SomeoneTellSaudiArabia [7]
— anoof (@anoofesh) November 12, 2013 [40]