· ግንቦት, 2013

ታሪኮች ስለ ኢትዮጵያ ከ ግንቦት, 2013

የበይነመረብ ዘመቻ በኢትዮጵያ ስለ ሰላማዊ ሰልፍ እና ዴሞክራሲ

  10 ግንቦት 2013

ዞን ዘጠኝ ተብሎ በሚጠራው የጦማሪዎች እና አራማጆች ኢ-መደበኛ ቡድን አስጀማሪነት በርካታ የኢትዮጵያ ማኅበራዊ አውታር ተጠቃሚዎች ከሚያዝያ 30 እስከ ግንቦት 2/2005 ድረስ የዘለቀ የበይነመረብ ዘመቻ አድርገው ነበር (የዘመቻው ጋዜጣዊ መግለጫ እዚህ አለ)፡፡ ዘመቻው ለቡድኑ ሦስተኛው ሲሆን፣ ‹‹ዴሞክራሲን በተግባር እናውል፤ የሰላማዊ ሰልፍ መብት ይመለስ›› የሚል መሪ ቃል ላይ ተንተርሶ መንግሥት ‹‹በቀጥታና በተዘዋዋሪ›› እያደረገው ነው የተባለውን እገዳ ነገር ግን በኢትዮጵያ ሕገ መንግሥት የተፈቀደውን ‹‹ሰላማዊ ሰልፍ የማድረግ፣ የመሰብሰብና አቤቱታ የማቅረብ መብት›› ራሱ መንግሥት እንዲያከብረው የሚጠይቅ ዘመቻ ነበር፡፡ በዘመቻው የተለያዩ ጦማሮች የተጻፉ ሲሆን፣ በተወሰኑ ሰዓቶች ልዩነት አብዛኛው የዘመቻው ተሳታፊ የሚያጋራቸው አጫጭር ጽሑፎች ተለጥፈዋል፣ ተሳታፊዎች ለዘመቻው የተዘጋጀውን የፕሮፋይል ምስል እንዲቀይሩ ተጋብዘው እንደተጠየቁት አድርገዋል፣ የዘመቻውን ሒደት እንዲከታተሉ የዘመቻው የኹነት ገጽ ተፈጥሯል፣ ባለፉት ዓመታት ውስጥ የተከለከሉ ሰልፎች የጊዜ መሥመር ተዘጋጅቶ ታትሟል፤ በተጨማሪም በአንድ ደቂቃ ተኩል ቪዲዮ መብቱ ለዜጎች እንዲከበር ተጠይቋል፡፡ ከፌስቡክ በተጨማሪም በትዊተር ላይ #Demonstration4Every1 እና #Assembly4Every1 በሚሉ ኃይለ ቃሎች ተሳታፊዎች ሐሳባቸውን ገልጸዋል፡፡