ታሪኮች ስለ አመጽ ከ መስከረም, 2012

ኢራን ጎግል እና ጂሜል እንዳይታዩ አገደች

እገዳው የተላለፈበተት ምክንያት ህዝቡ ብዙዎች እንደ ስድብ ቃል የሚያዩት በዩቱዩብ የሚገኘውን ጸረ እስላም ፊልም እንዲቃወሙ ነው (ዩቲዩብ የጎግል ንብረት ነው)፡፡ ኮራማባዲ “የወንጀል ይዘት ያላቸው ቅጽበቶች ድንጋጌ ኮሚሽን” ቁልፍ አባል ናቸው፡፡ ይህ በእንዲህ እንዳለ እንዳንዶች የጎግል መታገድ እውነተኛው ምክንያት ከመስከረም 22 ጀምሮ ስራ ይጀመራል ተብሎ የሚጠበቀውን እስካሁን ግን ብቅ ያላለውን የኢራናውያን ብሔራዊ በየነ መረብ የበለጠ ለማስተዋወቅ ነው ሲሉ ከወዲሁ ግምታቸውን አስቀምጠዋል፡፡

ቻይና፤ የሳንሱር ማሽኗ ለፀረ-ጃፓን እንቅስቃሴ ሲባል ቆመ?

  18 መስከረም 2012

በቻይና እና በጃፓን መካከል የዲያኦዩ (ወይም በሌላ ስሙ ሰንካኩ) ደሴት ባለቤትነት ይገባኛል ሲያይል፣ በቻይና ባለፈው ሳምንት መጨረሻ ላይ ከ80 በላይ በሚሆኑ ከተሞች መጠነ ሰፊ ፀረ-ጃፓን ሰልፎች ተካሂደዋልል፡፡ አንዳንዶቹ ሰልፎች ወደብጥብጥ ተሸጋግረዋል፤ ነውጠኞቹ በጃፓን ስታይል የተሰሩ ምግብ ቤቶችን፣ የመገበያያ አዳራሾችን እና ሱቆችን አጥቅተዋል፣ እንዲያውም አንዳንዶቹ የጃፓን መኪናዎችን ለማቃጠል ሞክረዋል፡፡ የመስመር ላይ እንቅስቃሴዎች የቅርብ ክትትል በሚደረግበት እና የመንግስት ደህንነት ኃይሎች በከፍተኛ ሁኔታ በሚተገበርበት አገር፣ ብዙዎች ይህን ያህል አመጽ እንዴት ሊከሰት እንደቻለ ተገርመዋል፡፡

ዮርዳኖስ: ፓርላማው በይነመረብን የሚገድብ አዋጅ የሚያጸድቅበት ቀን ሐዘን

አዲሱ ሕግ በይነመረብን ቅድመምርመራ እና ቁጥጥር የሚያጋልጥ ነው፤ የድረአምባዎች (websites) ባለቤቶችን በመንግስት እንዲመዘገቡ እና ‹‹ልክ እንደሌሎቹ ሕትመቶች›› ፈቃድ እንዲያወጡ ይጠይቃል፡፡ የድረአምባዎች ባለቤቶች አንባቢዎቸው ድረአምባዎቻቸው ላይ ለሚለጥፏቸው አስተያየቶች ሳይቀር ኃላፊነቱን ይወስዳሉ፡፡