ታሪኮች ስለ ሰብዓዊ መብቶች

የኦሮሞ ሙዚቀኞችን የማፈን አሳፋሪ ገመና

  8 ጥር 2016

የመንግሥት ሳንሱርን ለመስበር አማራጭ ይዞ የመጣውን ኢንተርኔት በመጠቀም፣ በዚህ ጽሑፍ ጸሐፊ ዩቱዩብ እና ፌስቡክ ላይ በተደረገ ቆጠራ ብቻ ከ300 በላይ ፖለቲካ ነክ ዘፈኖች ከ2006 ወዲህ የተለቀቁ መሆኑ የፖለቲካ ዘፈኖች መነሳሳት አለ ብሎ ለማለት ያስችላል፡፡

ኢትዮጵያውያን #SomeoneTellSaudiArabia በሚል ስደተኞች ላይ የደረሰውን እርምጃ ተቃወሙ

ጥቅምት 25፣ 2005 ሳኡዲ አረቢያ በሕገወጥ ስደተኞች ላይ እርምጃ መውሰድ ጀመረች፡፡ ሳኡዲአረቢያ 7 ሚሊዮን የሚሆኑ የውጭ ዜጋ ሠራተኞች እና ቤተሰቦቻቸውን አስጠልላለች ተብሎ ይታመናል፡፡

ቪዲዮ፤ “ኖ ዉማን፣ ኖ ድራይቭ” ሳኡዲ አረቢያን አደመቃት

ዛሬ፣ ጥቅምት 16፣ 2006 ለሳኡዲ አራማጆች በኪንግደሙ ሴቶች መኪና እንዳይነዱ የተጣለባቸው ማዕቀብ ላይ ለማመጽ የመረጡት ቀን ነበር። የማኅበራዊ አውታር ተጠቃሚዎች በአገሪቷ ውስጥ መኪና እየነዱ ስለታዩት ሴቶች ቁጥር መጨመር በስፋት እያወሩ ሳሉ፣ ተወዳጁ፣ የቦብ ማርሌይ “ኖ ዉማን፣ ኖ ክራይ” የተሰኘ ዜማ ሴቶችን በነጻነት የመንቀሳቀስ መብታቸውን ለመንፈግ የወጣ የወግ አጥባቂ ስርዓተ ፆታ...

ኢራን፤ እንደወንድ እየሆንክ፣ እንደሴት ልበስ

ቀይ ቀሚስ ሻርፕ እና ዓይነ እርግብ ያደረገ አንድ ሰው በማሪቫን ከተማ መንገዶች ኩርዲስታን ግዛት ኢራን ውስጥ በፀጥታ አካላት እየታጀበ እንዲጓዝ ተደረገ፡፡ በቤት ውስጥ ፀብ ምክንያት ጥፋተኛ የተባሉ ሦስት ሰዎች በከተማው መሐል የሴት ቀሚስ አድርገው እንዲጓዙ የግዛቲቱ ፍርድ ቤት ፈርዶባቸዋል፡፡ የቅጣቱ ዓይነት ለብዙዎች ግልጽ ባይሆንም በርካቶች ግን በቅጣቱ እንዲቆጡ አነሳስቷል፡፡

ጅቡቲ፤ ‘ዲሞክራሲያዊ’ ምርጫን ተከትሎ የመጣው እስር

  11 ሚያዝያ 2013

ትንሽ አገር ነገር ግን በአፍሪካ ቀንድ እጅግ በጣም ስትራቴጂክ አገር በሆነችው ጅቡቲ የየካቲት 15፣ 2005 አገር አቀፋዊ ምርጫን ተከትሎ በተደረገ የተቃውሞ ሰልፍ የተቃዋሚ ፓርቲ መሪዎች ታሰሩ፡፡ በምርጫው ‹የሕዝቦች አንድነት ለዕድገት› (People's Rally for Progress) የተሰኛው ፓርቲ በድጋሚ ድልን ተቀዳጅቷል፡፡ ፕሬዝዳንት እስማኤል ኡመር ጉሌህ ጅቡቲን እ.ኤ.አ ከ1999 ጀምሮ የመሩ ሲሆን በምርጫውም የ80 በመቶ መራጮች ድምፅ ቢያገኙም በከፍተኛ ሁኔታ በማጭበርበር ተጠርጥረዋል፡፡ እስሩ የመጣውም በዚሁ ማጭበርበር ጉዳይ [fr] ላይ ዜጎች ሰልፍ በመውጣታቸው ነው፡፡ እንደየጅቡቲ ሰብኣዊ መብት ሊግ እና የዓለምአቀፍ ሰብኣዊ መብት ፌደሬሽን ከሆነ 90 ሰዎች በአሰቃቂነቱ በሚታወቀው ጋቦዴ ማዕከላዊ እስር ቤት ታጉረዋል፡፡ እስሩ ይህ ጽሑፍ እስከተጻፈበት ሚያዚያ 20005 ድረስ ቀጥሏል፡፡

እ.ኤ.አ.2012፤ የፍራንኮፎኖች አብዮት እና ማኅበራዊ ለውጥ ዓመት፡- ክፍል 1

  12 ጥር 2013

2012 አልቋል፤ እናም ለፍራንኮፎን (የፈረንሳይ ቅኝ [የነበሩ]) አገራት የተረጋጋ 2013 በጉጉት ይጠብቃሉ፡፡ በ2012 በማሊ፣ በኮንጎ ዴሞክራቲክ ሪፐብሊክ (ኮንጎ) እና በሴንትራል አፍሪካ ሪፐብሊክ ውስጥ የትጥቅ ትግል ተካሂዷል፡፡ በሴኔጋል፣ ኩዊቤክ እና ፈረንሳይ ደግሞ ምርጫ ተካሂዷል፡፡ በቻድ፣ ማዳጋስካር እና ቶጎ ደግሞ ለውጥን የሚጠይቁ ሕዝባዊ የተቃውሞ ሰልፎች ተካሂደዋል፡፡ በርካታ ክርክሮች ስደትን፣ ምጣኔ ሀብታዊ ቀውሶችን እና እኩል የጋብቻ መብቶችን በተመለከተ ተደርገዋል፡፡ እነዚህ ሁሉ የሆኑት ዓበይት ለውጦችን ለማምጣት ሲሆን መረጃ በመለዋወጥ ዘዴ ነው፡፡

“V for Vendetta” የተሰኘው ፊልም ሳንሱር አለመደረግ ቻይናውያንን አስደመመ

  22 ታሕሳስ 2012

V for Vendetta የተሰኘው እና እ.ኤ.አ. በ2005 የተሠራው፣ ስለተበደሉ ማኅበረሰቦች የሚያወራ ልብ አንጠልጣይ ፊልም ቀድሞ በቻይና እንዳይ ታግዶ የነበረ ቢሆንም ባለፈው ባለፈው አርብ ታኅሳስ 5/2005 በቻይና የማዕከላዊ ቴሌቪዥን ጣቢያ (CCTV) ስድስተኛው ጣቢያ ታይቷል፡፡ በተለይም የመንግሥታትን ጭቆና ለመቃወም በመላው ዓለም ጭቆናን የመቋቋም ትዕምርት ሆኖ በአራማጆች የተመረጠው ‘V’ ሳይቆረጥ/ሳይወጣ መታየቱ በርካቶችን አስደምሟል፡፡.

ኢትዮጵያ፤ የተባበሩት መንግስታት ድርጅት የሰብዓዊ መብት ምክር ቤት አባል ለመሆን ትመጥናለች?

  16 ሕዳር 2012

በህዳር 12 2012 እ.ኤ.አ. የተባበሩት መንግስታት የሰብዓዊ መብቶች ምክር ቤት አባላት ሆነው ከተመረጡ አራት የአፍሪካ ሀገራት ውስጥ ኢትዮጵያ አንዷ ነች፡፡ ለመጪዎቹ ሶስት አመታት የተመረጡ ሌሎች ሀገራት አርጀንቲና፣ ብራዚል፣ ኮትዲቯር፣ ኢስቶኒያ፣ ጋቦን ፣ ጀርመን፣ አየርላንድ ፣ ጃፓን፣ ካዛኪስታን፣ ኬንያ ሞንቴኔግሮ፣ ፓኪስታን፣ የኮሪያ ሪፐብሊክ፣ ሴራሊዮን፣ የተባበሩት አረብ ኢመሬት፣ አሜሪካና ቬንዙዌላ ናቸው፡፡