ታሪኮች ስለ Culture

ቪዲዮ፤ “ኖ ዉማን፣ ኖ ድራይቭ” ሳኡዲ አረቢያን አደመቃት

ዛሬ፣ ጥቅምት 16፣ 2006 ለሳኡዲ አራማጆች በኪንግደሙ ሴቶች መኪና እንዳይነዱ የተጣለባቸው ማዕቀብ ላይ ለማመጽ የመረጡት ቀን ነበር። የማኅበራዊ አውታር ተጠቃሚዎች በአገሪቷ ውስጥ መኪና እየነዱ ስለታዩት ሴቶች ቁጥር መጨመር በስፋት እያወሩ ሳሉ፣ ተወዳጁ፣ የቦብ ማርሌይ “ኖ ዉማን፣ ኖ ክራይ” የተሰኘ ዜማ ሴቶችን በነጻነት የመንቀሳቀስ መብታቸውን ለመንፈግ የወጣ የወግ አጥባቂ ስርዓተ ፆታ...

የ‘ወንድም ጋሼ’ አፍሪካዋ ቤቲ ላይ የባሕል እሴት ጥያቄ ተቀሰቀሰባት

  9 ሰኔ 2013

የ‘ወንድም ጋሼ’ አፍሪካ (Big Brother Africa) የተሰኘው የእውነተኛ የኤቴሌቪዥን ትዕይንት የዘንድሮው (እ.ኤ.አ. 2013) ኢትዮጵያዊት ተሳታፊዋ መምህርት ቤቲ (Betty) ከሴራሊዮናዊው ተሳታፊ ቦልት (Bolt) ጋር ወሲብ ፈፅማለች የሚለው ዜና ከወጣ ጀምሮ ኢትዮጵያውያን በሁለት ወገን የጦፈ የባሕል እና የሞራል ጥያቄዎችን በማንሳት እየተሟጎቱ ነው፡፡

የአንድ ቬንዙዌላዊ አገርበቀል ዩንቨርስቲ ውስጣዊ ምልከታ

የሚያድጉ ድምጾች  20 መጋቢት 2013

የቬንዙዌላ አገርበቀል ዩንቨርስቲ ተማሪ መሆን ምን ይመስላል? ከትምህርታዊ ተግባቦት የወጡ ሦስት ተማሪዎች በእያደጉ ያሉ ድምፆች ትዕይንተ ሥራ ላይ ዲጂታል ፎቶዎችን እንዴት ማንሳት፣ በይነመረብ ላይ መስቀል እና ማጋራት እንደሚቻል ለመማር ተሳትፈው ነበር፡፡ እነዚህ ሦስት ተማሪዎች፣ በዚህ ልዩ ዩንቨርስቲ ውስጥ ከቬንዙዌላ ማኅበረሰብ የተውጣጡ እና በይነባሕላዊ እና ተግባራዊ የትምህርት ዓይነቶችን እንዲለዋወጡ የሚደረገው ጥረት ማሳያ ናቸው፡፡ በመንግሥታዊው ኢንፎሴንትሮስ [es] የተሰኘ ፕሮግራም በተዘጋጀው የዩንቨርሲቲውን የሳተላይት ግንኙነት በመጠቀም ተማሪዎቹ እንቅስቃሴዎቻቸውን፣ ንብረቶቻቸውን እና አስደናቂ ውበት የተላበሰውን እና በቦሊቪያ ውስጥ 2,000 ሄክታር ላይ የተንጣለለውን ካምፓሳቸውን በበይነመበረብ አጋርተዋል፡፡

የግራዚያኒ ኀውልት ግንባታን የተቃወሙትን መንግሥት መቃወሙ የድርዜጎችን አነጋገረ

  19 መጋቢት 2013

መጋቢት 8/2005 ሰማያዊ ፓርቲ ከባለራዕይ ወጣቶች ማኅበር ጋር በመሆን የግራዚያኒን ኀውልት ግንባታ እንዲቃወሙ ኢትዮጵያውያንን ለሰልፍ ጠርቶ ነበር፡፡ ጄኔራል ግራዚያኒ ኢጣልያ ኢትዮጵያን ለአምስት ዓመታት ያክል በወረረችበት ጊዜ በርካታ ኢትዮጵያውያን እንዲጨፈጨፉ ምክንያት የሆነ ሰው ነው፡፡ በተለይም የካቲት 12/1937….. የተገደሉት ሰማዕታት ኀውልት ስድስት ኪሎ በሚባለው አካባቢ ይገኛል፡፡ ሰልፈኞቹ ከዚያ ተነስተው ወደ ጣልያን ኤምባሲ ማምራት ሲጀምሩ ያልተጠበቀ ተቃውሞ ከመንግሥት አካላት ገጠማቸው፡፡ በቦታው 43 ያክል ሰልፈኞች ታፍሰው ለእስር መዳረጋቸው አነጋጋሪ ዜና ለመሆን በቅቷል፡፡

የአድዋ ድል በዓል ጦማሪዎችን አነቃቅቶ አለፈ

  6 መጋቢት 2013

ጥቁር አፍሪቃውያን አውሮጵያውያንን ለመጀመሪያ ጊዜ በጦርነት ያሸነፉበት የአድዋ ድል 117ኛ ዓመት በዓል የካቲት 23/2005 በብሔራዊ ደረጃ ተከብሮ ውሏል፡፡ የበዓሉ አከባበር በብሔራዊ ደረጃ እዚህ ግባ በሚባል ዓይነት ሥነ ስርዓት ባይከበርም በርካታ ጦማሪዎች፣ አስተያየቶቻቸውን በመጻፍና በማኅበራዊ አውታር ገጾቻቸው ላይ በማስፈር የበዓሉን ለዛ ጠብቀው ለማለፍ ሞክረዋል፡፡

እ.ኤ.አ.2012፤ የፍራንኮፎኖች አብዮት እና ማኅበራዊ ለውጥ ዓመት፡- ክፍል 1

  12 ጥር 2013

2012 አልቋል፤ እናም ለፍራንኮፎን (የፈረንሳይ ቅኝ [የነበሩ]) አገራት የተረጋጋ 2013 በጉጉት ይጠብቃሉ፡፡ በ2012 በማሊ፣ በኮንጎ ዴሞክራቲክ ሪፐብሊክ (ኮንጎ) እና በሴንትራል አፍሪካ ሪፐብሊክ ውስጥ የትጥቅ ትግል ተካሂዷል፡፡ በሴኔጋል፣ ኩዊቤክ እና ፈረንሳይ ደግሞ ምርጫ ተካሂዷል፡፡ በቻድ፣ ማዳጋስካር እና ቶጎ ደግሞ ለውጥን የሚጠይቁ ሕዝባዊ የተቃውሞ ሰልፎች ተካሂደዋል፡፡ በርካታ ክርክሮች ስደትን፣ ምጣኔ ሀብታዊ ቀውሶችን እና እኩል የጋብቻ መብቶችን በተመለከተ ተደርገዋል፡፡ እነዚህ ሁሉ የሆኑት ዓበይት ለውጦችን ለማምጣት ሲሆን መረጃ በመለዋወጥ ዘዴ ነው፡፡

“V for Vendetta” የተሰኘው ፊልም ሳንሱር አለመደረግ ቻይናውያንን አስደመመ

  22 ታሕሳስ 2012

V for Vendetta የተሰኘው እና እ.ኤ.አ. በ2005 የተሠራው፣ ስለተበደሉ ማኅበረሰቦች የሚያወራ ልብ አንጠልጣይ ፊልም ቀድሞ በቻይና እንዳይ ታግዶ የነበረ ቢሆንም ባለፈው ባለፈው አርብ ታኅሳስ 5/2005 በቻይና የማዕከላዊ ቴሌቪዥን ጣቢያ (CCTV) ስድስተኛው ጣቢያ ታይቷል፡፡ በተለይም የመንግሥታትን ጭቆና ለመቃወም በመላው ዓለም ጭቆናን የመቋቋም ትዕምርት ሆኖ በአራማጆች የተመረጠው ‘V’ ሳይቆረጥ/ሳይወጣ መታየቱ በርካቶችን አስደምሟል፡፡.

የመለስ ዜናዊ የሙት መንፈስ ኢትዮጵያውንን እያሳደደ ነው?

  30 ሕዳር 2012

የቀድሞው ጠቅላይ ሚኒስትር መለስ ዜናዊ የት ይሆኑ ይሆን በሚለው ላይ ወራት የዘለቀው ግምት አቧርቶ በ57 ዓመታቸው ከዚህ ዓለም በሞት እንደተለዩ በመደበኛ መንገድ ከተገለጸ ወዲህ ሦስት ወራት ተቆጥረዋል፡፡ ቢሆንም የመለስ ዜናዊ የሙት መንፈስ በአዲስ አበባ እና በሌሎችም ዋና ዋና ከተሞች እና የገጠር መንደሮች አውራ ጎዳናዎች ላይ በተሰቀሉ ምስሎቻቸው ኢትዮጵያውያንን አጥብቀው የያዙበት እጃቸው የመላላት አዝማሚያ አላሳየም፡፡

‘ለሙሰኛ ባለስልጣን ምንም ምሕረት የለም’

  13 ሕዳር 2012

የጨፌ ኦሮሚያ የዜና ምንጮቻችን ለአዲስ ነገር እንዳስታወቁት አቶ አባዱላ ገመዳ ከጠ/ሚ መለስ ዜናዊ ጋር የነበራቸው የሰመረ ግንኙነት ከተበላሸ (ፖለቲካዊ ጠቀሜታቸው ዝቅ ካለ) በኋላ ላለፉት በርካታ ዓመታት በእርሳቸው ሥም፣ በቤተሰቦቻቸውና በወዳጅ ዘመዶቻቸው አካባቢ ያከማቹትን ሃብት በጥሬ ገንዘብ፣ በአይነትና በንብረት በታማኝ የኦህዴድ ፓርቲ አባላትና በደህንነት ሠራተኞች ሲሰባሰብ ነበር፡፡ . . .”

ኬንያ፤ ራሳቸውን ገንዘብ-ይገዛናል ብለው ያሉ ቡድኖች ‘የካምፓስ ቀውጢ-ቺኮችን ለሀብታሞች’ አቀረቡ

  12 ጥቅምት 2012

የካምፓስ ቀውጢ-ችኮች ለሀብታሞች (Campus Divas For Rich Men) ከ26 ዓመት በታች የሆኑ የኬንያ የዩንቨርስቲ ሴት ተማሪዎችን በማንኛውም ዕድሜ ክልል ውስጥ ያሉ ሀብታሞች ‘ለማጣበስ’ የተፈጠረ የፌስቡክ ገጽ ነው፡፡ ገጹ የተጠቀመበት መሪ ቃል “ገንዘብ-ይገዛናል” የሚል ነው፡፡